Current political, socio-economic and human rights issues.
Moderators: ዘበኛ ፩, ዘበኛ ፫, ዘበኛ ፪, ዘበኛ ፬
by ዞብል2 » Wed Feb 15, 2017 2:11 am
"ዋናው ጠላታችን ድረገፅ እና ይሄ ፌስ ቡክ የሚሉት ነገር ነው፡፡ እሱን ካጠፋን የህዝብን ድምፅ በቀላሉ ማፈን እንችላለን፡፡"
በረከት ስምዖን(ቦቸራ)
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Wed Feb 15, 2017 9:54 pm
በመልሶ ማልማትና በተለይ <<በህገ ወጥ ግንባታ>> ስም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የጎዳና ተዳዳሪ የሆኑ በየጊዜው በሚደርስባቸው ጫናና ማስፈራሪያ የዞታቸዉን በወረደ ዋጋ እየሸጡ ወደ ዳር የወጡ(አንዳንዶችም ደብዛቸው የጠፋ)አሉ ይህን ከብልሹ አሰራርና ኢፍትሐዊነት ውጪ ማን ያደርገዋል ሌላው ይቅር በቅርቡ (በክረምት ዝናብ) የሐና ማርያምና የቦሌ ወረገኑ 30ሺሕ ሰዎች መፈናቀል የሚጠየቅ ሰው ጠፋ!? አሳፋሪ ነው፡፡
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by እሰፋ ማሩ » Thu Feb 16, 2017 1:20 pm
ወያኔዎች የሰው ቦታ ሲቀሙ ልማት ይሉታል የድሃውን ቤት ሲያፈርሱ ግን ህግወጥ ግንባታ መከላከል ይሉናል፡፡
ዞብል2 wrote:በመልሶ ማልማትና በተለይ <<በህገ ወጥ ግንባታ>> ስም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የጎዳና ተዳዳሪ የሆኑ በየጊዜው በሚደርስባቸው ጫናና ማስፈራሪያ የዞታቸዉን በወረደ ዋጋ እየሸጡ ወደ ዳር የወጡ(አንዳንዶችም ደብዛቸው የጠፋ)አሉ ይህን ከብልሹ አሰራርና ኢፍትሐዊነት ውጪ ማን ያደርገዋል ሌላው ይቅር በቅርቡ (በክረምት ዝናብ) የሐና ማርያምና የቦሌ ወረገኑ 30ሺሕ ሰዎች መፈናቀል የሚጠየቅ ሰው ጠፋ!? አሳፋሪ ነው፡፡
-
እሰፋ ማሩ
- ዋና ውሃ አጠጪ

-
- Posts: 1550
- Joined: Mon Sep 12, 2016 8:47 pm
by ዞብል2 » Fri Feb 17, 2017 2:11 am
<<ራበኝ>>ያለውን ህዝብ ጠግቦአል ብሎ ካድሬው ሪፖርት ሲያቀርብ፡<< ልማታዊ ጋዜጠኛ፤ አርንጋዴ ቀዬ ቀርፆ የእነገሌ ሰፈር በዕድገት ጎዳና!>>ብሎ ከበሮ ሲደልቅ ሕዝቡ እያለቀሰ፤ መንግስት ፌሽታ እየረገጠ ኖረ፡፡....ሀገሪቱ ም በሪፖርት ሰማይ ነካች፡፡....ሰው እየፈረሰ ....ፎቆች ተገነቡ፡፡ፎቆቹ የማናቸው? ሌላ ጥያቄ ነው፡፡ ግን ህዝቡ ውስጥ ውስጡን ተከፋ፡፡ በታችኞቹ ተማሮ የበላይ ዘንድ ሲሄድ <<እዚያው ይጨርሱልህ!>እያሉ እንደ ቅሪላ ከወዲያ ወዲህ ጠለዙት፡፡
ምሬቱ ሲገነፍል ብድግ አለ፡፡ያን ጊዜ<<የነ እንትና ተላላኪ ተባለ>>፡፡ የከፋውን ሰው፤ብሦትየጫረውን ሕዝብ ማን ሊልከው ይችላል?እራሱ እኮ ነው የነደደው!...በሬዲዮና በቴሌቪዥን የጠገበ፤በገሀድ የተራበና አንጀቱ ያረረ ሕዝብ ሆ! ብሎ ቢወጣ ምን ይገርማል? ይልቁንስ ቀጣዩ ምንድነው ???????
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by እሰፋ ማሩ » Fri Feb 17, 2017 2:21 am
ወገን ዞብል2
የነዚህ ማፊያ እኩይ ወያኔዎችን ድራማ በሚገባ ዘግበሃል፡፡
ይልቁንስ ቀጣዩ ምንድነው ?
ብሦትየጫረው ህዝብ ያስቸኩዋይ አዋጅ እንዳሳወጃቸው የሚቀብራቸው ዘመን ቀርቧል፡፡
ዞብል2 wrote:<<ራበኝ>>ያለውን ህዝብ ጠግቦአል ብሎ ካድሬው ሪፖርት ሲያቀርብ፡<< ልማታዊ ጋዜጠኛ፤ አርንጋዴ ቀዬ ቀርፆ የእነገሌ ሰፈር በዕድገት ጎዳና!>>ብሎ ከበሮ ሲደልቅ ሕዝቡ እያለቀሰ፤ መንግስት ፌሽታ እየረገጠ ኖረ፡፡....ሀገሪቱ ም በሪፖርት ሰማይ ነካች፡፡....ሰው እየፈረሰ ....ፎቆች ተገነቡ፡፡ፎቆቹ የማናቸው? ሌላ ጥያቄ ነው፡፡ ግን ህዝቡ ውስጥ ውስጡን ተከፋ፡፡ በታችኞቹ ተማሮ የበላይ ዘንድ ሲሄድ <<እዚያው ይጨርሱልህ!>እያሉ እንደ ቅሪላ ከወዲያ ወዲህ ጠለዙት፡፡
ምሬቱ ሲገነፍል ብድግ አለ፡፡ያን ጊዜ<<የነ እንትና ተላላኪ ተባለ>>፡፡ የከፋውን ሰው፤ብሦትየጫረውን ሕዝብ ማን ሊልከው ይችላል?እራሱ እኮ ነው የነደደው!...በሬዲዮና በቴሌቪዥን የጠገበ፤በገሀድ የተራበና አንጀቱ ያረረ ሕዝብ ሆ! ብሎ ቢወጣ ምን ይገርማል? ይልቁንስ ቀጣዩ ምንድነው ???????
-
እሰፋ ማሩ
- ዋና ውሃ አጠጪ

-
- Posts: 1550
- Joined: Mon Sep 12, 2016 8:47 pm
by ዞብል2 » Sat Feb 18, 2017 9:50 pm
" ከምርት ዕድገት ጋር ባልተጣጣመ መንገድ፤ኢኮኖሚው ውስጥለሚረጨው ጥሬ ገንዘብ ምንጮቹ ብሔራዊ ባንክ እንዲሁም በመንግስት ትዕዛዝ ጭምር ገንዘብ በገፍ የሚያበድረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ናቸው፡፡ በተለይ እነዚህ ሁለት ባንኮች ኢኮኖሚው ውስጥ በሚያንቀሳቅሱት ገንዘብ ምክንያት የዋጋ ንረት እየጨመረ በመምጣቱ፤ የኢትዮጵያ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት በጊዜው ዋጋ ከነበረበት 60ቢሊዮን ብር ገደማ፤በአሁኑ ጊዜ 1.5ትሪሊዮን ብር በላይ መድረሱ፤በግልፅ ለማስቀመጥ ያደገው ምርት ሳይሆን፤ የዋጋ ንረት ነው!፡፡
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Wed Mar 01, 2017 1:14 am
''ወያኔዎች መላኩ ተፈራን የመሰለ ገዳይ የጎንደርን ህዝብ ገላገልነው ይላሉ፡ ሀቁ ግን ወያኔ ሌላው መላኩ ነው፡፡ እንዳውም ከመላኩ የከፋ ነው፡፡መላኩ የገደለው ሰውን ነው፡፡ወያኔ ግን ሰውም ሀገርም ገዳይ ነው፡፡ መላኩ አንድን ዘር ነጥሎ አልገድለም፡፡ የገድለው ትግሬውን፤ አማራውን ፤ኦሮሞውን፤ጉራጌውን...........ወዘተ በጅምላ ነበር፡፡
"ወደ መተማና ሁመራ እንዲሁም ወልቃይት በቀን ሠራተኝነት ለጫንቃው ጨርቅ ለእግሩ መጫሚያ ሳይኖረው ወደ ጎንደር ተሰዶ የነጠነጠ ሃብታምና፤ እዚያው ለማዳ ሆኖ የቀረው ትግሬ ነው፤ዛሬ አፉን ሞልቶ ወልቃይት የትግሬ ነው የሚለን!፡፡
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Wed Mar 01, 2017 8:42 pm
"ሰቲቱ ሁመራ ወልቃይት ጠገዴ
ከመቶ ዓመት በፊት ትግሬ ነበር እንዴ!?
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Thu Mar 02, 2017 2:20 am
"ባንኮች ምንም እሴት ላልፈጠሩና ለመፍጠርም ችሎታውና ክህሎቱ ለሌላቸው ግለሰቦች ትልልቅ ፎቆች መስሪያ የሚሆን ብድር በትዕዛዝ የሰጣሉ፡፡እዚህ ላይ ትዕዛዝ ሰጪው፤የባንክ ባለስልጣኖችና ብድሩን የሚወስዱት ሶስቱም ወገኖች በሙሰኛነት ይፈረጃሉ፡፡ፎቅ ሠሪዎቹ ድሆችን ከቀያቸው አፈናቅለው(በልማት ሥም) ከመንግስት መሬቱን በከፍተኛ ዋጋ ገዝተው ፎቆቹን ይሰራሉ.........ይቺ ናት ጨዋታ..... የወያኔ የልማት ጨዋታ!!!!
ዛሬ በልማት ስም እየተደረገ ያለው ሰውን ከተወለደበትና ካደገበት ቀዬው በማፈናቀል የኔው የሚለው ወይም የሚያስታውሰው ነገር እንዳይኖር እየተደረገ ነው፡፡
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Sun Apr 23, 2017 8:36 pm
የሰለሞን ዕፅ ነሽ
የቅዱሳን ዕንባ ያበቀለሽ ቅጠል
ዛሬ አዲስ እይደለም
በለኮሰው እሳት የነካሽ ሲቃጠል!!
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by ዞብል2 » Wed Apr 26, 2017 1:03 am
"በሙስና እንደ ተበከለና ብቃት እንደ ሌለው መንግስት ያለ ለሰው ልጆች ብልፅግና ፀር የሆነ ነገር፤ በዚህ ዓለም ላይ ጨርሶ የለም"
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by humaidi » Wed Apr 26, 2017 3:36 am
ዞብል2 wrote:"ሰቲቱ ሁመራ ወልቃይት ጠገዴ
ከመቶ ዓመት በፊት ትግሬ ነበር እንዴ!?
ወዳሻህ ብትገፋው ወደ የትም
ሲቲት ሁመራ ወልቃይት ጠጌ መባሉ አይቀርም !
-
humaidi
- ዋና ውሃ አጠጪ

-
- Posts: 1741
- Joined: Tue Jan 03, 2006 11:50 am
by humaidi » Wed Apr 26, 2017 3:41 am
ዞብል2 wrote:የሰለሞን ዕፅ ነሽ
የቅዱሳን ዕንባ ያበቀለሽ ቅጠል
ዛሬ አዲስ እይደለም
በለኮሰው እሳት የነካሽ ሲቃጠል!!
እምዮ ኢትዮጵያ ያላቃጠልሸው የለም በሎከሰው እሳት
ኢትዮጵያን እንኳን ደሰ ያላት በወያኔ ልማት !!!!!
-
humaidi
- ዋና ውሃ አጠጪ

-
- Posts: 1741
- Joined: Tue Jan 03, 2006 11:50 am
by ዞብል2 » Wed May 03, 2017 1:01 am
ጠርጥሮ የሚይዝህ፤
የሚመረምርህ፤
ዓቃቤ ህግ ሆኖ የሚከስህ፤
ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤
ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤
በሙሉ ነፍሰ በላ ወያኔ ነው!!
-
ዞብል2
- አለቃ

-
- Posts: 2368
- Joined: Fri Jan 30, 2004 11:23 pm
by humaidi » Wed May 03, 2017 1:51 am
ጠርጥሮ ቢይዝህ
ገርፎ ቢመረምርህ
ዓቃቢ ህግ አያሰፈልግህ
ጸረ ኢትዮጵያ ነህ
ዳኛም ሆነ ጠበቃ ሸማግሌም አያሰፈልግህ
ሌላም ጊዜ እንዳይለምድህ
ወያኔ ይቅጣህ
-
humaidi
- ዋና ውሃ አጠጪ

-
- Posts: 1741
- Joined: Tue Jan 03, 2006 11:50 am
Return to Warka Politics - ዋርካ ፖለቲካ
Who is online
Users browsing this forum: No registered users and 2 guests