የቆሎ ተማሪው wrote:ጨቅላነት ደርዝ አውጥቶ፣
ቆዳ ለብሶ አፀጉርቶ፤
መቀመጫ ስበንለት መኸለኛ ሆኖ፣
ተኮፍሶ፤ ጋሽ-ማሙዬ ተዘባኖ፤
ግላጭ ውሎ ግላጭ ሲያድር፣
እሱም ላይሰቅቀው ራሱን ላይሰውር ፣
እየተመቻቸ ወንበሩ ላይ ሲያንቡዋችር፣
እኛም ነጠላ እያጣፋን ስናደገድግ
እንደስጋጃ ተነጥፈን ሽቅብ ስናሰግግ
በደረታችን ስንሳብ ጎድለን ከሰው-ማረግ
ጋሼ-ማሙሽ ምንተዳዬ ተዳልቶ
ደርዝ አውጥቶ ቆዳ ለብሶ አጸጉርቶ
ተኮፍሶ ተዘባኖ
ቀላምዶ አመካክኖ
ዘመኑን አዘምኖ
አጉሮን በጉሮኖ
አልሸት አለን ፋኖ…
Return to Warka Culture and Literature - ዋርካ ባህልና ሥነ ጽሑፍ
Users browsing this forum: Google Adsense [Bot] and 3 guests