ውጪ ሀገር
ነገሩን ለማያቅ ውጪ የሚባለው ስሙ ቢያስደስትም
ውስጡ ለቄስ ይሁን እንደስሙ አይደለም
ብዙ ቢባልለት አኗሪ አንቀባሮ
የተወለወለ ቢያስመስል ብርሌ ገጽን አሳምሮ
ባይታይ ነው እንጂ ብዙው ከውስጥ ጠቁሮ
በደስታ ደህይቶ ይኖራል እሮሮ
አይ የውጭ አገር ኑሮ!!!
ምረቱ
ዋናው wrote:ሠላም ምረቱ...
ሠሞንኛ የዋርካ ቀሽም አቢዮት በተነሳሳበት ጊዜ ሆኖ'ንጂ እቺ ቤት ሸላይ ናት:: የባለ ስድስት የወል ቤት የበዛበት ስንኞች ከዋርካዊያን ገጣሚዎች ዘንድ ብዙ ጊዜ አይታይም.... እናም ያንተይቱ ስንኝ ሹረባ የጥበቡን ዘርፍ መልክ አብዝቶ ከማቆንጀትም .... (ቀሽት) ነው::
ቃላት ይርቡልህ ብያለው
Return to Warka Culture and Literature - ዋርካ ባህልና ሥነ ጽሑፍ
Users browsing this forum: No registered users and 4 guests