by HD » Tue Aug 03, 2010 8:20 pm
ዑዑዑፍፍፍፍፍፍፍ,, ዛሬ ጎፈሬያችን ሹርባ ይሰራለታል ተብሏል,, እዚህ ውስጥ ጸጉር መስራት የምትችሉ?? እስኪ እጃቹን ወጣ ወጣ አርጉ,, ቂጣቹን ፈንደድ ፈንደድ :lol: :lol: ሸዋዬዎች ሰላም ናቹ? አዳዲስ አራዶች ተጨምረውልኝ አሁንማ እንደ ልቤ ነው የምሳፈጣቹ,, ዘይ ጋት ማይ ባክ :wink: አንተ One-Now አለህ? እስኪ ደሞ ስለ ድሮው የኔና ያንተ ታሪክ ልደስኩር,, ትዝ ይልሀል ያኔ ለቡሄ? እኛ ሆያሆዬ ልንጨፍር እናንተ ቤት ስንመጣ? አንተ ሆያሆዬ አትጨፍርም ነበር ,, እህትህ ለእንቁጣጣሽ አበባየሁሽ ልትጨፍር ስትወጣ አንተን ይዛ ትወጣ ነበር,, የሰፈሩ ሰው ''ልጃገረዶች መጡ'' እያሉ ኮይን ምናምን ሊሰጧቹ ሲወጡ አንተን አይተው እንደዛ እንድልደከሙብህ,, :lol: :lol: አንተ የአዱ ገነታችን አሰዳቢ,, አዲስ አበባን የቆረቆሩት ዘመዶቼ ናቸው አልሽ,, እሺ የእቴጌ ጣይቱ የልጅ ልጅ :lol: :lol: ልዑል ሸዋዬ :lol: :lol: ግርማዊነቶ,,አንተ የሰራተኛ አጫዋች,, 24/7 ቤት ውስጥ ተዘግቶብህ እኛ ውጪ በሰፈራችን ጭውቴውን ስናደራው አንተ በቀዳዳ ስትቃኝ :lol: አሁን አንተ የአዲስ አበባ ልጅ ነኝ ትላለህ? ካንተ እንደወረደ ጨምጫሚ ይሻላል አቦ,, እሱ እንኳን ባይሆን ቆቅ እያባረረ, ፍየላቸውን እየነጨ ስሜቱን እያረካ ምናምን ነው ያደገው,, ጨምጬክስ ሰላም ነው? አይ ጨምጬክስ ይሄ ሰውዬ እኮ አቦ በናትሽ በጠበጠን,, ፍየላቹን አውሰውና እስኪ ስሜቱን ያርካ,, ኤድስ የለባትም አደል? :lol: :lol: እናቱነኝለትና ይሄ ሙሽሪት አቋም,, ዛሬ በናታቹ የመጬ ጠሮብኛል, ጭቅጭቅ አምሮኛል :lol: እስኪ ወደ አንዱ የአበሻ ሬስቱራንት ሄጄ ወደ በሁዋላ እቧጨቃለው,, እንጀራዋ ቀጠነች,, ወጥ ጨምሩልኝ ምናምን እያልኩ አለ አይደል የጭቅጭቅ ጥማቴን እወጣለው,, እኛ አበሾች እኮ ግን የጭቅጭቅ ሱስ አለብን :lol: :lol: እናቴ ትሙት,, ይሄ ነገር ታድያ አራዶችንም ሆነ ሸዋዬዎችን ይመለከታል,, ድሮ እኛ ሰፈር የነበሩ አሮጊቶች እንዲሁ ጭቅጭቅ ሲያምራቸው ወደ ሰፈራቸው ያለ ሱቅ ይሄዱና ''የተከፈተ ኦሞ ሸጥክልኝ'' , ''የተቦረቦረ ሳሙና ነው'' , ''ቃርያው በደንብ አያቃጥልም'' እያሉ ባለሱቁን ሲነዘንዙት ይውላሉ,, ብታዩ እኮ ሆን ብለው ለጭቅጭቅ ተዘጋጅተው ነው የሚሄዱት,, ታድያ እዛ ሰፈር ያሉ ሸምሱዎች ምናምን በቃ ሱቅ የሚሸጥ ሲቀጥሩ ጭቅጭቅ የሚችል ምናምን ነው የምቀጥሩት,, የጭቅጭቅ ነገር ሲነሳማ እኮ አቤት እዛ ጌጃ ሰፈር እያለሁ የነበረው ጭቅጭቅ :lol: :lol: እንደምታውቁት የኛ ሰው አብሮ መብላት እንደሚወድ ሁሉ አብሮ ማራትም ይወዳል,, :lol: የጋራ ሽንትቤት ነው ያለው ለማለት ነው :lol: ታድያ ሽንት ቤቱ የሞላና መመጠጥ ያስፈለገ ጊዜ ነው ጦርነት ከች የሚለው,, አዋጥተው ስለሚከፍሉ አልኳቹ በቃ ''እኔ ሶስት ቀን ብቻ ነው ያራሁት'' :lol: :lol: ምናምን እያሉ ላለመክፈል ሲጨቃጨቁ ይውላሉ,, አንዳንዴ ''አንቺ ባራሽው እኔ ልክፈልልሽ'' ሲባባሉማ በቃ ድክም ነው የምንለው አልኳቹ,, በተለይ አንድ የሆኑ ግቢማ መዝገብ አዘጋጅተውላቹ ሽንትቤት በተኬደ ቁጥር ይመዘገባል :lol: :lol: በሉ መጣሁ እኔም ልሂድና ልጨቃጨቅ,, ኮስተር ብዬ ሄጄ ነው የምጨቃጨቀው,, ሌሎቻቹም እንዲሁ ስትረስ ያለባቹ አንዳንዴ ጭቅጭቅ ጥሩ ነው,, ሂዱና ተጨቃጨቁ :lol:,, አንተ One-Now አንተም ሂድና ሰራተኛቹን ጨቅጭቅ,, :lol: