በመጀመርያ ደረጃ ለተከበረው ወንድማችንለፕራጉ ፈረሰኛ ለአባ ፈርዳ የከበረ ሰላምታየን ሳቀርብ አውቶግራሙን አክሎ የስራው ውጤት የሆነውን ስራውን በስጦታ በራሱ ገንዘብ መላክያውን ከፍሎ ባድራሻዬ ይኼንን የአበሻ ጀብዱ የሚሉትን ድንቅ የታሪክ መጽሀፍ ስለላከልኛ በስጦታ ለክብርነታችን ስላበረከተልን እጅግ የላቀ ወንድማዊ በፍቅር የተለወሰ ምስጋናዬን ለአባፈርዳ በዚህ አጋጣሚ ሳቀርብ በኩራት ነው::
አባ ፈርዳ ይኼንን ድንቅ መጽሀፍ በስጦታ መልክ ስለሰጠኸኝ እግዚአብሄር ይስጥልኝ::መቼም እንደተጫወትነው ይኽንን መጽሀፍ ለመተርጎም ምን አልባት ከደራሲው ከሚስተር አዶልፍ ፓርለስካ የበለጠ እንጂ ያልተናነሰ ጉልበት እንዳወጣኽ ነው:.ምን አልባት ይኸንን የታሪክ መጽሀፍ አንባቢዎች ሲያነቡ እንደወረደ የተረጎምከው ይመስላቸው ይሆናል.....መቼም በስልክ እንደተጫወትነውና ተይቄኽ እንደነገርከኝ ደራሲው በራሳቸው ቋንቋና ባህላዊ ዘይቤ የጻፉትን መጽሀፍ አንተ ደግሞ በዛን ወቅት በኢትዮዽያዊያን ባህልና የአነጋገር ዘይቤ ቀይረኽ ለመጻፍ ስትል ብዙ ጉልበቶችን እንዳወጣኽ ነው::እውነቴን ነው የምልው ድካምህ ከሚገርም ውጤት ጋር ተሳክቶለታል ነው የምልኽ::ፈረንጅ የጻፈው መጽሀፍ ሳይሆን አበሻ እዛው ሆኖ ለዛውም አንተው እራስኽ እዛው ሆነኽ የጻፍከው ነው የሚመስለው::ታድያ በዚህ ልትኮራ ይገባሀል::
መጽሀፉ መቼም ምንም የማይወጣለት ሰላዊ መግለጫው የትየለሌ የሆነና ያንን ወቅት በአይነ ህሊናችን እንድናይ የሚረዳ መጽሀፍ ስለሆነ ለደራሲውና ላንተ ለተርጎአሚው ከፍተኛ አድናቆቴን አቀርባለሁ::
በመቀጠል ጌታና እንሰት ይኸንን መጽሀፍ አግኝተው ለማንበብ በጣም መጉዋጉዋታቸውን ስላየሁ ባለፈው ሰሞን እዚህ በሳምንት አንዴ እንደ ባግዳድ የምቆጣጠረው ራድዮ ጣብያችን ላይ ከመጽሀፉ ውስጥ አንድ ምእራፍ ነቅሼ አንብቤ ነበርና ጌታና እንሰት መጽሀፉ እጃችሁ እስኪገባ ድረስ ያለውን የወረወረ ....እንደሚባለው ያለኝን አካፍያችሁዋለሁና በሉ ከታች የምለጥፈው ሊንክ ጋር ተጠነቋቁላችሁ አድምጡ::
በዚህ አጋጣሚ ከቴርቶጋዳ ቀጥሎ ኢትዮድያ ውስጥ ትልቅ ቦታ ተሰጥቶት ስለ ድንቅነቱ የሚወራው መጽሀፍ ይኼ የአዶልፍ ፓርለስካና የ አባ ፈርዳ መጽሀፍ መሆኑንና ከህጻን እስከ ትልቁ አንብብ ብሎ የሚመክርህ መጽሀፍ የአበሻ ጀብዱን እንደሆነ በምስክርነት እናገራለሁ:.(ፕሮፌሰር መስፍን ይኼንን መጽሀፍ በሚገባ ማድነቃቸውን ያስታውሷል)
የሀበሻ ጀብዱን ለማዳመጥ ይኸንን ተጭነው ከዛ Audio 1ንድ የሚለውን ይጫኑ ይጫኑ
መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ::
ሾተል ነን