WARKA Forum Index  
 FAQFAQ   SearchSearch   MemberlistMemberlist   UsergroupsUsergroups   RegisterRegister 
 ProfileProfile   Log in to check your private messagesLog in to check your private messages   Log inLog in 

ዋርካ ቻት - በአማርኛ በቀጥታ ይወያዩ! Warka Live Chat | Home (New!) | About us | Contact us
በዚያን ግዜ

 
Post new topic   Reply to topic    WARKA Forum Index -> Warka General


 
View previous topic :: View next topic  
Author Message
ቁምቢ

ጀማሪ ኮትኳች


Joined: 26 Nov 2012
Posts: 83

PostPosted: Thu Dec 20, 2012 10:54 pm    Post subject: በዚያን ግዜ Reply with quote

ሰላም ዋርካውያን በፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶ የተጻፈውን በዚያን ግዜ የተሰኝውን መፅሀፍ በትንሹም ቢሆን እዚ ልተርክላችሁ ...........እጅግ አስገራሚና አሳዛኝ ታሪኮችን የያዘ መጽሀፍ ነው ::

እንግዲህ መጽሀፍ እንዲህ ብሎ ይጀምራል ....
ሚያዝያ 10 1968 , በጸሎት ቤቱ ውስጥ በአምልኮ ላይ የነበሩ ምዕመናን ባዳዳሲ እንግዶች በድንገት ተከበቡ .........ከዚያም እንዲወጡና በከተማይቱ ዋና ዋና መንገዶች ላይም ተሰልፈው እንዲሄዱ ታዘዙ ..........አስገዳጆቹም በወቅቱ የነበረው የቀበሌ አመራርና ወጣቶች ነበሩ ..........የእምነት ጥላቻው በተግባር በታገዘ ጠንካራ ተቃውሞ ተገለጠ ::

በእለቱ የነበረው ዙረት ሲያበቃ የተያዙትን ምዕመናና አገልጋዮችን ወደ ቀበሌ ስምንት ወሰዷቸው ................በእጆቻቸውም የተገኙትን መጽሀፍ ቅዱሶች በመሰብሰብ ጋዝ ካርከፈከፉባቸው በኃላ አቃጠሏቸው ......ከዚያም ጭሱን "ታጠኑት !" አሉዋቸው .........

1970 አጋማሽ ላይም በምዕመናኑ ላይ ቀላል የማይባል ስደት ደርሷል .........በዚያን ግዜ አንዳንድ እህቶቻችን መንገድ ላይ ተጥለው እንደ እባብ ጭንቅላታቸውን ተቀጥቅጠዋል ............ሌሎች ደግሞ በደረሰባቸው ከፈተኛ ድብደባ የተነሳ እራሳቸውን እየሳቱ ለሕክምና እርዳታ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል ......በተጨማሪም እንደነ ተፈሪ ኬላ አለማየው መንግስቱ ያሉ .........በሰደፍ እየተፈነከቱ ደማቸው የታሰሩበትን ክፍል አጥለቅልቆታል ..

ከፓሊስ ጣቢያው እንደወጣን .......በአውራው ጎዳና ላይ ፊታችንን ወደ ምዕራብ አድርገን ጥቂት እንደተራመድን .....ሶምሶማ ሩጫ ጀምሩ የሚል ትዕዛዝ ተሰጠን .....መሮጥ ጀመርን ::..........ጥቂት እንደሮጥን አልማዝ አስሟ ተቀስቅሶ አመማትና ወደ ኃላ ቀረች .......ሙሉ እመቤትም ብትሆን የኛን ያህል መሮጥ ስላልቻለች ተራርቀን አየው ..........ፍጥነቴን ለመቀነስ ሞከርኩኝ ወንዶቹ እያጣደፉ አስቸገሩን .::........እንደምንም ኳስ ሜዳ ደረስን ::.............ትእዛዙም ሩጥ ! ተመለስ ! ተኛ ! ተንከባለል ! አሞራ ጉብ ጉብ ዝለል ! በሚል እየተፈራረቀ ተፋፋመ ::.........ይህ ሁሉ ትዛዝ ከዱላ ከጉማሬና ከእርግጫ ጋር ያጣድፈን ገባ ::

ስፓርቱ ወታደራዊ ቅጣት ማለት ይሻላል ብዙ ታሪክ ነበረው ::........በስፓርት ስም ማንገላታቱ እየደበደቡና እየረገጡ ማሰቃየት እንዲሁም በጭቃ ላይ እያንከባለሊ መጫወት ሁሉም ጋር የተደረገ ሲሆን ለየት የሚሉ ጥቂት ድርጊቶች አልጠፉም ::..........በቀበሌ 01 ለየት የሚለው ሌሊት ሌሊት ወደ ወንዝ ወስዶ በቀዝቃዛ ውሀ ውስጥ መንከርና ከዚያም አውጥቶ በአቧራ እንዲለወሱ ማድረጉ ነበር ..............እነ ከበደ አርጋው .አየለ አበራ . ማርታና ሀና አሰፋ የተባሉ እህትማማቾች የዚህ ጽዋ ተካፋዮች ነበሩ ::...

በቀበሌ 05 የነበሩትን ግን 12 ቀናት ያህል አልፈቷቸውም .....ከሌሎች ስፍራዎች ይልቅ መከራው ተጠናክሮ የተራዘመው እነሱ ጋር ነበር ማለት ይቻላል .......ጫካ እያወረዱ በየገደሉ ላይ እያንከባለሉ ነበር የተጫወቱባቸው ........ከዚህ ሁሉ ጋር ዱላውና እርግጫው ርኅራኄ የማይታይበትና ፋታ የማይሰጥ ነበር ::.........ከኃይሉ በቀለ ሌላ ምንትዋብ አረሩ በድብደባ ብዛት እራሷን ስታ ስታጓራ አስደንጋጭ ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር ..... ይቀጥላል ...
_________________
የሰው ልጅ
መውደድ ሲችል መጥላቱ
መምከር ሲችል ማማቱ
መስራት ሲችል መቅናቱ
ማስታረቅ ሲችል ማጣላቱ
ያሳዝናል የሰው ፍጥረት በሕይወቱ፥፥
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
Display posts from previous:   
Post new topic   Reply to topic    WARKA Forum Index -> Warka General All times are GMT + 1 Hour
Page 1 of 1

 
Jump to:  
You cannot post new topics in this forum
You cannot reply to topics in this forum
You cannot edit your posts in this forum
You cannot delete your posts in this forum
You cannot vote in polls in this forum


Provided by CyberEthiopia.com , powered by phpBB © 2001, 2005 phpBB Group , Original Amharic translation by Ethiopic Open Source Translation modified by CyberEthiopia