View previous topic :: View next topic
Author
Message
ክቡራን Joined: 04 Mar 2008 Posts: 4256
Posted: Wed Jan 02, 2013 7:38 pm Post subject: ቤተ እግዚአብሄር ሄጄ አልቅሼ ተመለስኩ ::
መቼም ነገራችን ሁሉ ከጅብ ቆዳ የተሰራ ይመስል ወሬአችን ሁሉ ብላው ብላው ብላው ..አኡውውውውውው ..ማለት ሆኗል :: አትታዘቡኝና የሰው ጅቦች ሆነናል :: ያዲሱን አመት መግቢያ በጽሞና ለማሳለፍ , እግዛኢብሄር በሁለት ሺ አስራ ሁለት የሰራሁትን ኅጢያት ይቅር እንዲለኝና ሁለት ሺ አስራ ሶስትን በድል እንዲያሸጋግረኝ ንስህ ለመግባት ወዲህም አምላኬ አመቱን ሙሉ ላደረገልኝ ጥበቃ ምስጋናን ለማቅረብ ዲሴምበር 31ለጃንዋሪ 1 ወ -ዋዜማ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነበርኩ :: እኔ ከራሴ ጋር ከእጊዚአብሄር ጋር ተነጋግሬአለሁ :: አምላኬም ሲንሰር የሆነውን ጸሎቴን ሰሞቶኛል :: እሪ ብዬ ያለቀስሉት ግን አስተማሪው በመድረክ ላይ የሚሉትና እኔ የማውቀው መጽሀፍ ቅዱስ አንድ አልሆን ብለውኝ ነው :: ሰውየው ( ፓስተር እንዳልላቸው የሚያወሩት ስለ ራሳቸው ነው ...) ""ከድንጋይ እርሙታ ከወጀብ ጋጋታ ያወጣኝ አምላክ ዛሬም ጠላቶቼ በኔ ላይ የሚያሴሩትን ሴራ ይበትነዋል .."" ሲሉ እኚህ ሰውዬ ወዴት እየሄዱ ነው ?? አልኩ ...እሳቸው ጠላት የሚሏቸው በኅሳብ ካልተስሟሟቸው የቤተ ክርስቲያኑ ኮንግርጌሽን አባላት ጋር በገቡት እንኪያ ሰላምታ መሆኑን የጋበዘኝ ጔደኛዬ በኌላ አጫወተኝ :: እኚህ ፓስተር በመጽሀፍ ቅዱስ ፋንታ ጔንዴ ቢኖራቸው ከደቀ መዝሙሩ ጀመረው እስከ አሸሩ ድረስ ያሉትን ጌታ አዞኛል ብለው ባንዳንድ ጥይት ሊለቅሟቸው እንደሆነ መንፈስ አሳየኝና እሪ አልኩ :: እረ እሳቸውም ቆይተው ተናገሩት "" ...ድሮ አባቶታችን የሚያናድዳቸው ሰው ወይኔ ላንተ አንድ ጥይት ነበር የሚበቃህ ይሉት ነበር ..."" በማለት መንፈስ ለኔ ያሳየኝን አጸኑልኝ :: እንዲህ ናት ስብከት !! አይ አንቺ ዶላር !!!! ስንቱን ባህል አልባ አደርገሽው !! መጣሁ ..እስኪ የታዘብኩትን እነገራችኌለሁ :: እንድንማማር ነው ይሄን ያመጣሁት እንጂ ከቶውንም ለማማት አይደለም :: የወንድሜ ዲጎኔ መንፈስ ምን ሊያስብ እንደሚችል ቀድሜ ስለማውቅ ነው ይሄን የምለው :: _________________http://www.ethiopianthisweek.com
http://www.ethioonutube.com
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ክቡራን Joined: 04 Mar 2008 Posts: 4256
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
የተሞናሞነው Joined: 11 May 2011 Posts: 1126
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ክቡራን Joined: 04 Mar 2008 Posts: 4256
Posted: Fri Jan 04, 2013 5:43 am Post subject:
መቼም የሆነውን ነገር መናገሬ ለጉራ አይታይብኝ እንጂ አስቀድማቹ ጽድቁን ፈልጉ ሌላው ሁሉ ይጨመርላችኌል የሚለው ቃል ጠጅ ቤት ገብቶ ሞቅ ያለው ዲያቆን ተሳስቶ የተናገረው አይደለም :: የመጽሀፍ ኅቅ ነው አስተዋይ ልብ ላለው ቡዙ ነገርም ገላጭ ነው :: እናም ግድየላቹም እቺ አመት ሳትሆነኝ አትቀርም ... ባዲሱ አመት የእጊዚአብሄርን ፊት ለመሻት አይኖቼን ወደ ሰማይ አቅንቼ እንደነበር ገልጪ ነበር ... አይኖቼን ወደ መሬት ስመለስ አልማዝን አገኘኌት :: አልማዝን አይቼ አልማዝን ሳያት ሁለተኛዋ አልማዝ ብትመጣ ድንገት ሁለቱም አልማዞች ... ይበቃል ... .
ላንድ አመት እቺን ልጅ ሰፈልጋት ነበር :: በልቤ በጣም እመኛት ነበር ...ግን እሷም ቢዚ ናት ውበቷ በራሱ ክፋቷ ነበር :: ፈላጊዋ ቡዙ ሆነ :: አንዱም እኔ ነበረኩ :: የምችለውን ያህል ሞከርኩ :: ካላት ቢዚ ስኬቹአል እንደምፈልጋት ላገኛት አልቻልኩም :: በመኅል አገር ቤት እናቷ ታማመች ተባለና ሄደች ::እኔም ተስፋ ቆረጥኩ :: አንድ ቀን ስካያፕ ላይ ተገናኝን አንጠፋፋ ስትመጪ ደውዩ አልኩ :: በልቤ ግን ""ባፋንኩሎ ""! ብያታለሁ :: አልዋሻችሁም ...እሺ እደውልላሀለሁ አለች ....ኝ እንደማታደርገው ስላወኩ እሺታውን ለታይታ ያህል ተቀበልኩ ::
ልክ ያዲሱ አመት እለት ስልክ ደወለችልኝ ..
""...እንኴን አደርሰህ ልልህ "" ነው ...አለችኝ :: ደስ አለኝ እኔም አጸፋውን መለስኩ :: ብትፈልግ ዛሬ ምሽት መገናኘት እንችላለን አለችኝ ...ከሌሎች ሰዎች ጋር ቀጠሮ ነበረኝ ...አላመነታሁም እሺ አልኩ የነሱ ይደርሳል :: ብነግራቸው የሚያስቸግሩኝ አይደሉም አቢሰኒኢያ ሬስቶራንት ተቃጠርን :: ድሮም ቀይ ናት ከቅላቷ ጋር የሚሄድ ቀይ የእራት ልብስ ከላዩ ላይ ጠቆር ያለ ሹራብ አድርጋ ራሷን ሊያስገባ ትንሽ የሚቀረው ሰማያዊ ቦርሳ ይዛ መጣች :: ለለወጥ ያህል ቀይ ሊፒስቲክ ሳይሆን ወደ ፒንክ ከለር የሚያደላ የከንፈር ቀለም ተቀብታለች :: ስትገባ ተመጋቢውም ከምግቡ ላይ ቀምቃሚውም ከመጠጡ ቀና እያለ ሲገርመማት ""ቫይቡ "" ተሰሞቶኛል :: እረ ዘፋኙም እሷ ስትገባ የባሰ ድምጹን ሳያጮሀው አይቀርም :: ውቅያኖስ ዳር እንደተተከለች ዘምባባ ዘንጠፍ ቀና እያለች በቀጥታ እኔ ወዳለሁበት ጠረጴዛ ስትደርስ ብድግ ብዬ እንደ ተነፋፈቁ ፍቅረኞች ተቃቀፍን :: በልቤ አስቀድማቹ ጽድቁን ፈለጉ የምትለዋ ጥቅስ ጆሮዬ ላይ አንቃጨለችብኝ :: ሜርድ :: ባለፈው አመት ስፈልጋት ቢዚ ሆኗ ተስፋ የቆረጥኩባት ልጅ ዛሬ ሁለታችን ብቻ በመከካላችን በሚበራው የጠረጴዛ ሻም እየተያየን በነጻነት መጫወት ጀመርን :: እንዲህ የፍቅርን አበባ እየቀነጣጠስን ባለንበት ሰአት አንድ አርግራጊ ( ጀብራሬ ) ነገር ለመደንስ ወደ መድረኩ ሲወጣ የሚጠጣውን ውስኪ የያዘ ብርጭቆ እኛ ጠረጰዛ ላይ እንደ ቀልድ አስቀምጦ እሽሩሩ በሚለው የፍሬው ዘፈን መወረገረግ ጀመረ :: እሷ ሳቅ አለች :: እኔ አልሳኩም ፈገግ አልኩ :: ቴክ ኢስ ኢዚ አይነት ነገር ...ይቅርታም አለመጠየቁ አስገርሞኛል ...ዘፈኑ ሲያልቅ ብርጭቆውን መጥቶ ይወስዳል ብዬ ስጠብቅ እንደውም ወደ ሬስት ሩም ሄደ ::
"" ታውቂያዋለሽ እንዴ ??"" ...አልኴት ..
""እረ እኔ ይሄን የት ነው የማውቀው ..?" አለችኝ ...
""እንግዲያው ሊለክፍሽ ፈልጎ ነው አልኩ .."" ስሜቷን ለመረዳት ፊቷን ትክ ብዬ አያየሁ ...
""ውይ ድንቄም ለከፋ !!"" አለች ከንፈሯን ጣል ስታደርገው አንድ ነገር በውስጤ ሲላወስ ተሰማኝ :: ልጅቷ ውብ ናት ውብ መሆኗን እሷም ታውቅወአለች :: አንድ ጊዜ እንደውም ክሊፕ የሚሰሩ ሰዎች ለሆነ አጭር ሾው ሰው ከፈለጉ ወይም ከሰማህ ንገረኝ .."" ብላኝ ነበር ...ውብ መሆኗን እሷም ታውቅዋለች ::
ይሄ ሁሉ ሲሆን ልጁ መጠጡን እኛ ጋ ትቶ እሱ ባንኮኒ ጋ ሄዶ ሌላ መጠጥ አዞ አየሁት :: አስተናጋጇን ጠርቼ መጠጡን ወስዳ አጠገቡ እንድታስቀምጠው እግረ መነገዷንም ሂሳቡን በደንብ እንድታሰላ በጆሮዋ ሹክ አልኰት :: ""ግርግር ለሌባ ይመቻል "" ስላት ሳቅ ያዛት :: ዘፋኙ ዘፈኑን ጨርሶ ከመድረኩ ሲወርድ ይሄው ቀዌ በመጥጥ ትኩሳት ""ጌታ ይባርክህ ..."" ጌታ ይባርክህ .."" !! አያለ ዘፋኙን ሲያደድንቅ ሰማሁት ::
""እንዴ ይሄ ልጅ ጴንጤ ነው እንዴ ?" አልኴት ..
የምታስተናግደውን ልጅ .
""ውይ አይደለም ...ባይገርምህ ከዚህ ቤት አይለይም ..ደንበኛችን ነው .....ሱማሌ ነው ...የኢትዮጵያ ሱማሌ ነው አለችኝ ...!! ....!! እኔ ግን አትታዘቡኝና ""ጌታ ይባርክህ ሲል ወንድሜ ዲጎኔ ባካል የመጣብኝ ነው የመሰለኝ ...በዚህ ላይ ደሞ ሱማሌ ነው ስትለኝ ወንድሜ ዲጎኔ እኮ ድሮ በኒ ሰፈር እያለ ቁራን እቀራ ነበር ስላለ እሱ መሆን አለበት እያልኩ ማሰቤ አልቀረም ነበር ::
ካስቲ ጋ ሌላ ቀጠሮ የሚመጣው እሁድ አለኝ :: ግድየላቹም ይቺ አመት የኔ ሳትሆን አትቀርም .....ሰላማት !! _________________http://www.ethiopianthisweek.com
http://www.ethioonutube.com
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator