View previous topic :: View next topic
Author
Message
CyberEthiopia Joined: 21 Jul 2003 Posts: 36
Posted: Fri Feb 17, 2012 2:12 am Post subject: የተከበራቹሁ የዋርካ ታዳሚዎች
ውድ የዋርካ ተሳታፊዎች፦
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዋርካ ጀነራል ላይ በጥቂት ግለሰቦች በተለይም ሀይማኖትን የሚመለከቱ አስጸያፊ እና ያልተገቡ መጻጽፎች የዋርካን ህግ እና ስርዐት የጣሱ ሆነው ስላገኘናቸው አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።
ስለሆነም ውድ የዋርካ ተሳታፊዎቻችን የየትኛውንም ሀይማኖት የሚያጎድፉ ፣ያልተገቡና አስጸያፊ ጹሁፎችን ሪፖርትን እንድታደርጎ ስንል የተለመደውን ትብብራችሁን እንጠይቃለን።
የሳይበርኢትዮጵያ አስተዳደር
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
SAY-NO-TO-HATRED Joined: 12 Mar 2005 Posts: 1339 Location: united states
Posted: Fri Feb 17, 2012 2:24 am Post subject:
ውድ :ፈርሀ :እግዚአብሄር :ላላችሁ :ለዋርካ :አስተዳዳሪ :ወገኖቼ !...
ፈርሀ :እግዚአብሄር :ማሳየት :.....ድክመትና :...ድንቁርና :.....እንዳልሆነ :
አምናችሁበት :....ዋርካችን :...ፈርሀ :እግዚአብሄር :....እንዲኖራት :...
እርምጃ :ስለወስዳችሁ :.......እሱ :ፈጣሪ :....ሁሌም :ይለመናችሁ !....
ዋርካችን :ፈርሀ :እግዚአብሄርና :...ሞራል :የሰፈነባት :....ለማድረግ :
ጊዜ :....ጉልበትና :....ትእግስት :እንደሚጠይቅ :አንዳችንም :.....
አንጠራጠርም ::........ሰለዚህም :የሚሻለው :....በሌላው :አምድ :ስር :...
በአንድ :ወገኔ :እንደተጠቀሰው :....አንድ :ቁዋሚ :የሆነ :....አምድ :
ከፍቶ :....ክፉ :ጽሁፎች :....ሪፖርት :የሚደረጉበትና :....ከዛም :....እናንተ :..
ሁሉን :ከማንበብ :ይልቅ :....ያንን :የተለየ :...አምድ :በመጠቀም :ብቻ :..
......ዋርካችንን :ለማጽዳት :ይቀላል :....ብሎ :የጠቀሰውን :ወንድማችንን :...
ምክር :መጠቀም :.....እጅግ :ይጠቅማል :ብዬ :አምናለሁ ::...
......ውድ :የዋርካ :አድሚኖች :......ለምሳሌ :.....ተሳዳቢ :የብእር :ስሞች :
ብቻ :ሳይሆኑ :...ክፉ :የሀይማኖት :ጦርነት :...እያደረጉ :ያሉት :....ጥሩ :ስሞችን :...ተይዞም :.....አላህንና :ክርስቶስን :...
....ወዘተ :.....እየሰደቡ :ያሉ :....እንዳሉም :....ተረዱም ::.....ለዛ :ነው :..
......"መሰረዝ :የሚገባቸው :አምዶች :ሪፖርት :ማድረጊያ "....የሚል :
ቁዋሚ :ስቲኪ :አምድ :....ቢከፈት :....ሁሉን :ነገር :ያቀላል :ብዬ :...
አንድ :ወገኔ :ከእኔ :በፊት :ያቀረበውን :.......ግሩም :ሀሳብ :....ተቀበሉት :
በማለት :.....በትህትና :እለምናለሁ ::......
ዘወትር :አክባሪ :እህታችሁ :.....
እምቢ :ለጥላቻ
ነኝ .......... _________________ WE ARE NOW AMBASSADORS FOR OUR BELOVED COUNTRY AND ONE DAY WE WILL BE CITIZENS IN ETHIOPIA, ONCE AGAIN!!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ናፖሊዮን ዳኘ Joined: 18 Apr 2008 Posts: 1874
Posted: Fri Feb 17, 2012 2:44 am Post subject:
ምንም ነገር ላይ ስትጽፊ የምታሳይው ኢትዮጵያዊነት መንፈስ እና ፈሪሀ እግዚያብሄት ህሌም ያስደምመኛል ::
በጣም የተከበርሽ ኢትዮጵያዊ ነሽ ! ቅን የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ ታስታውሺኛለሽ ::
ረዥም እድሜ !
ናፖሊዮን ዳኘ ::
SAY-NO-TO-HATRED እንደጻፈ(ች)ው : ውድ :ፈርሀ :እግዚአብሄር :ላላችሁ :ለዋርካ :አስተዳዳሪ :ወገኖቼ !...
ፈርሀ :እግዚአብሄር :ማሳየት :.....ድክመትና :...ድንቁርና :.....እንዳልሆነ :
አምናችሁበት :....ዋርካችን :...ፈርሀ :እግዚአብሄር :....እንዲኖራት :...
እርምጃ :ስለወስዳችሁ :.......እሱ :ፈጣሪ :....ሁሌም :ይለመናችሁ !....
ዋርካችን :ፈርሀ :እግዚአብሄርና :...ሞራል :የሰፈነባት :....ለማድረግ :
ጊዜ :....ጉልበትና :....ትእግስት :እንደሚጠይቅ :አንዳችንም :.....
አንጠራጠርም ::........ሰለዚህም :የሚሻለው :....በሌላው :አምድ :ስር :...
በአንድ :ወገኔ :እንደተጠቀሰው :....አንድ :ቁዋሚ :የሆነ :....አምድ :
ከፍቶ :....ክፉ :ጽሁፎች :....ሪፖርት :የሚደረጉበትና :....ከዛም :....እናንተ :..
ሁሉን :ከማንበብ :ይልቅ :....ያንን :የተለየ :...አምድ :በመጠቀም :ብቻ :..
......ዋርካችንን :ለማጽዳት :ይቀላል :....ብሎ :የጠቀሰውን :ወንድማችንን :...
ምክር :መጠቀም :.....እጅግ :ይጠቅማል :ብዬ :አምናለሁ ::...
......ውድ :የዋርካ :አድሚኖች :......ለምሳሌ :.....ተሳዳቢ :የብእር :ስሞች :
ብቻ :ሳይሆኑ :...ክፉ :የሀይማኖት :ጦርነት :...እያደረጉ :ያሉት :....ጥሩ :ስሞችን :...ተይዞም :.....አላህንና :ክርስቶስን :...
....ወዘተ :.....እየሰደቡ :ያሉ :....እንዳሉም :....ተረዱም ::.....ለዛ :ነው :..
......"መሰረዝ :የሚገባቸው :አምዶች :ሪፖርት :ማድረጊያ "....የሚል :
ቁዋሚ :ስቲኪ :አምድ :....ቢከፈት :....ሁሉን :ነገር :ያቀላል :ብዬ :...
አንድ :ወገኔ :ከእኔ :በፊት :ያቀረበውን :.......ግሩም :ሀሳብ :....ተቀበሉት :
በማለት :.....በትህትና :እለምናለሁ ::......
ዘወትር :አክባሪ :እህታችሁ :.....
እምቢ :ለጥላቻ
ነኝ ..........
_________________ ሰው ህሊናውን የሚሸጠው ክህሊና በላይ ዋጋ ያለው ምን ነገር ሊገዛበት ነው?
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ተድላ ሀይሉ Joined: 17 Mar 2006 Posts: 4451 Location: ኢትዮጵያ
Posted: Fri Feb 17, 2012 2:45 am Post subject:
ውድ የዋርካ አስተዳዳሪዎች :-
በበኩሌ የጀመራችሁት ዋርካን ከመጥፎ : የአክራሪና ጽንፈኛ ኃይማኖቶች አስፋፊዎች የቅስቀሣ ጽሑፎች የማጽዳት ተግባር እንዲሣካላችሁ በበኩሌ የሚጠበቅብኝን ተሣትፎ ከማድረግ አልቆጠብም ::
እህታችን "SAY-NO-TO-HATRED" በድጋሚ እንዳሣሠበችው :-
1 ..... ይህንን ርዕስ በቋሚነት ከመጀመሪያ ተርታ ብታደርጉት : እንዲሁም
2 ..... ይህንን የውይይት ዓምድ የአክራሪ ኃይማኖቶችን የሚያራምዱ ጽንፈኞች የጦርነት አውድማ ለማድረግ ያለማሠለስ የሚፍጨረጨሩትን ተጠቃሚዎች ሥም ዝርዝር ለእናንተ ሪፖርት ለማድረጊያ እንድንጠቀምበት እንድትፈቅዱልን እጠይቃለሁ ::
ከአክብሮት ሠላምታ ጋር ::
ተድላ ሀይሉ _________________ የወያኔ ሕገ -አራዊት አንቀፅ 39 ኢትዮጵያን የመበታተኛ ፈንጂ ነው !
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
ተድላ ሀይሉ ዘብሔረ -ኢትዮጵያ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ዉቃው Joined: 07 Jan 2007 Posts: 968
Posted: Fri Feb 17, 2012 3:20 am Post subject:
አለን ! ሰላም ነው ? እንዴት ነው ? ምነው ተጠፋፋንሳ ?
አይ ...እኔ እንኳ ...አንድ ቋሚ ርዕስ ተከፍቶ ..መጠቆሚያ ይሁን በሚለው ሀሳብ አለመስማማቴን ለመግለጽ ነው :: እንዴ .... እሱማ 'ኮ ቀይ ሽብር ነው :: እንጨራረሳለን :: አይ .... እሱ አይሆንም :: ባይሆን ይህ ይደረግ ::
ያው ህገ -መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት ...ራሳችን ለማስተዳደር ምርጫ ይደረግ ..ይህ በዋርካ ፍቅር እና ባህል ነው :: ዋርካ ፖለቲካ እና ጄነራል ግን ገና ለምርጫ አቅማቸው ስላልደረሰ ...በፖለቲካው .. ሁለት ከኢሀዴግ : ሁለት ከቅንጅት : አንድ ከግንቦት ሰባት አንድ ከ ሻቢያ : አንድ ከኢፒአርፒ : አንድ ከኦነግ እና አንድ ገለልተኛ ሰው ተመርጠው ..ልክ እንደ አሜሪካ ሱፕሪም ኮርት በአምስት /ለአራት በሆነ ድምጽ ይተዳደሩ ::
ዋርካ ጄራልም እንዲሁ ይሁን :: ሁለት ከእስልምና : ሁለት ከኦርቶዶክስ : ሁለት ከስይጣኒዝም : ሁለት ከፕሮቴስታንት :ሁለት ከ ኤቲይዝም ሆኖ ..በተለዋጭ አባልነት ከቡድህ ብቸኛው አባል ደጉ ሆኖ ይተዳደር :: የበለጠ ድምጽ ያገኘው ሀሳቡ ይፈጸምለት ::
አላስፈላጊ ርዕሶች በድምጽ ብልጫ ይወገዱ :: ደራሲዎችም ይታገዱ :: ይህ ለዋርካ ፍጹም ሰላም ያመጣል
ዲሞክራሲ በተግባር ይሏል ይህ ነው ::
ይህ ፕሮፖሳል እኔን አይመለከትም :: አመሰግናለሁ ....አትጥፉ
Vote for Wuqqaw ! Governer of warka fikir and culture . _________________ ጉዟችን ረጅም : ግባችንም ሩቅ ነው !!!!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እንድሪያስ Joined: 19 Mar 2004 Posts: 2119 Location: *****
Posted: Fri Feb 17, 2012 3:56 am Post subject: Re: የተከበራቹሁ የዋርካ ታዳሚዎች
CyberEthiopia እንደጻፈ(ች)ው : ውድ የዋርካ ተሳታፊዎች፦
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዋርካ ጀነራል ላይ በጥቂት ግለሰቦች በተለይም ሀይማኖትን የሚመለከቱ አስጸያፊ እና ያልተገቡ
መጻጽፎች የዋርካን ህግ እና ስርዐት የጣሱ ሆነው ስላገኘናቸው አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።
ስለሆነም ውድ የዋርካ ተሳታፊዎቻችን የየትኛውንም ሀይማኖት የሚያጎድፉ ፣ያልተገቡና አስጸያፊ ጹሁፎችን ሪፖርትን እንድታደርጎ ስንል የተለመደውን ትብብራችሁን እንጠይቃለን።
የሳይበርኢትዮጵያ አስተዳደር
የተወደዳችሁ የዋርካ አስተዳዳሪዎች :- በዚህ አጋጣሚ የከበረ ሰላምታየ ይድረሳችሁ :: በሰጣችሁት ምላሽ በጣም ተደስቻለሁ :: እንደበፊቱ ዋርካን አዘውትሬ ባልጎበኛትም አልፎ አልፎ ግን ጎራ ማለቴ አይቀርም :: በገባሁ ቁጥር ታድያ በጣም ስነምግባር የጎደላቸው አርስቶች ያጋጥሙኛል ::እንደዚህ አይነት አፍራሽ ድርጊቶች የፎረማችን ህልውና ብሎም የሳይበር ኢትዮጵያን ስምና ዝና የሚፈታተኑ ናቸው ብየ ስለማምን ሁኔታው ያሳስበኛል :: ዋርካ የሁላችንም ንብረት ነችና እያንዳንዳችን ኃላፊነት የመውሰድ ግዴታ አለብን ብየ አምናለሁ :: ስለሆነም ሁላችንም አንድን ፅሑፍ በደንብ አንብበን ከመረመርነው በኋላ የፎረሙን ደንብና ህግ የሚጥስ መሆኑን ከአመንበት ሪፖርት እናድርግ ሥል በዚህ አጋጣሚ የፎረሙን ተሳታፊዎች በትህትና እጠይቃለሁ ::
እንድሪያስ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
የተሞናሞነው Joined: 11 May 2011 Posts: 1126
Posted: Fri Feb 17, 2012 4:41 am Post subject: Re: የተከበራቹሁ የዋርካ ታዳሚዎች
ጤና ይስጥልኝ የተከበሩ ስውር የዋርካ አስተዳደር /መሪ
እንዴት ነዎት ? ቤተሰብስ አማን ነው ?
ከምር ግን በቃ አለ አይደል ያለ አፈ -ጉባኤ ... ያለ ተሾመ ቶጋ እኛ የፓርላማው አባላት ሃይ ባይ አጥተን ይሄውልዎት ...
እኔ ልደቱ ቤንጤ ሆነሃል ተብዬ ታቦት ወጥቶ ዣንጥላ ተዘርግቶ ተወገዝሁ ኡ ኡ እኔ ማርያምን ኦርቶዶክስ ነኝ ሲል ...ወያኔ ደግሞ አንተ ከጥንትም ስናውቅህና ስንመርጥህ ሊበራል ሶስተኛ አማራጭ ተከታይ በሶስቱ ስላሶች አማኝ የቅዱስ ላሊበላ የልጅ ልጅ ንጡህ ኦርቶዶክስ ... ምንስ ሲሆን እንዲህ አይነት ስም ይሰጥሃል ? ይህንን ያደረገህ አባላችን ቆሻሻ ባለጌ ዱርዬ ነው እፈልገዋለሁ ከፊትህም አንቄ እደፋዋለሁ እያለች ልክ ያሰጣችውን የጓያ ክክ ዶሮሽ በላችብኝ ብላ የስድብ ናዳ እንደምታወርድ ኮማሪት ጲ ጲ ጲ ...እያለች የስድብ መአት ስታዥጎደጉድ ....
ተመስገን በየነ ስለ ኢኮኖሚ ፊስካል ፖሊሲ አንስቶ ወያኔን እንዴት አባሽ ይሄንን አለፍሽው እያለ አረፋ ሲያሰድፍቃት ...እሷ ደግሞ አይ 'ፊስካል ' እንጂ 'ፊዚካል ' አይደለም የሚባለው ብላ የፓርላማውን የኢኮኖሚ አጀንዳ የእንግሊዝኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ስታደርገው ...ተሜ ደግሞ በምላሹ አይ እንዳንች 'ፊስካል 'ን ለመጥራት ፓርላማው ውስጥ ማፏጨት አይጠበቅብኝም ... አንች እንደሆንሽ ይሄው ስታፏጭ ስንትና ስንት አመትሽ ...ይህ ግን የፉጨት ሳይሆን የፍጭት ቦታ ነው ሲላት
አሁንም ወያኔ ስለ ሶማሊያ ጉዳይ አሜሪካ ረድታሻለች ብር አግኝተሻል ይህንን እመኝ ስትባል ...እሷም ለጦርነት ጥይት ... ለግብረ -ስጋ ግንኙነት ደግሞ ኮንዶም ያስፈልጋሉ ስትል ...
በቃ አፈርሳታው እንዲህ እንዲህ እያለ ዋርካም ይህንን ሁሉ መሸከም አቅቷት ቅርንጫፎቿ ሊዘነጣጠሉና ሊወድቁ ስትል እርስዎ የዋርካው ተሾመ ቶጋ ከተሰዎሩበት ብቅ ብለው እንዲህ ጸጥታ ማስከበርዎን ሳላመሰግን አላልፍም
ልጅ ሞንሟናው
በጎዣም ክ /ሃገር በፓርላማ የቅንጂት ተወካይና
የስነ ጾታ ጉዳዮች ተጠሪ
CyberEthiopia እንደጻፈ(ች)ው : ውድ የዋርካ ተሳታፊዎች፦
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዋርካ ጀነራል ላይ በጥቂት ግለሰቦች በተለይም ሀይማኖትን የሚመለከቱ አስጸያፊ እና ያልተገቡ መጻጽፎች የዋርካን ህግ እና ስርዐት የጣሱ ሆነው ስላገኘናቸው አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።
ስለሆነም ውድ የዋርካ ተሳታፊዎቻችን የየትኛውንም ሀይማኖት የሚያጎድፉ ፣ያልተገቡና አስጸያፊ ጹሁፎችን ሪፖርትን እንድታደርጎ ስንል የተለመደውን ትብብራችሁን እንጠይቃለን።
የሳይበርኢትዮጵያ አስተዳደር
_________________http://yetemonamonew.wordpress.com/
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ባለሱቅ Joined: 27 Sep 2004 Posts: 1043 Location: ethiopia
Posted: Fri Feb 17, 2012 6:31 am Post subject:
ውድ አስተዳዳሪዎች
እስከዛሬ የት ነበራቹ .... ብዬ ልወቅሳቹ ነበር
ለማንኛውም ዘግይቶም ቢሆን ለተደረገው ፅዳት ከልብ እናመሰግናለን
እስኪ በነካካ እጃቹ ይህችን የኛን ቤት ,,,, ወደ -ዋርካ ባህልና ስነፅሁፍ ወይም ዋርካ ፍቅር ቤት ውሰዱልን (Moved) የሚለውን ቁልፍ ተጭናቹ
ወይም እንዴት እንደሚደረግ አሳዩንና
ከዚህ ከዋርካ ጀነራል ገላግሉን
ከምስጋና ጋር
የክብረመንግስትና አካባቢው ልጆች .... እንደራሴ
ባለሱቅ _________________http://www.cyberethiopia.com/warka4/viewtopic.php?t=11833&start=4680
THANK YOU CYBERETHIOPIA
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
መንፈሳዊው . Joined: 11 Feb 2012 Posts: 3
Posted: Fri Feb 17, 2012 7:24 am Post subject:
እኔ ሰሞኑን ኮሌጅ ነገር ጨርሼ ስራ እየፈለኩ ነው :: እናም ከተቻለ በኢንተርንሺፕ መልክ እዚ 24/7 ተሰክቼ የጽዳቱን ስራ ልከውንላቹ :: በስራዬ መርቅናቹ ቋሚ ተቀጣሪም ካረጋቹኝ እስየው ነው ::
ለነገሩ ለ 6 አመት በራስ አነሳሽነት ዋርካ ላይ ኢንተርን ሳደርግ ነበር አሁን ሊጂት እንዲሆን ያህል ነው
መንፈሳዊው የዋርካ ቀደምት ተገልጋይ እና ተጋዳላይ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ዲጎኔ Joined: 19 Aug 2005 Posts: 3830 Location: united states
Posted: Fri Feb 17, 2012 8:01 am Post subject:
ይድረስ ለተከበራችሁ የዋርካ አስተዳዳሪዎች
የሰማይ ስፋቱን የከዋክብት ብዛቱን ያህል እንደምን ናችሁ
እኔ ዲጎኔ ሞረቴው ክብር ለክርስቶስ በጣም ደህና ነኝ ::
ከሰላምታ ቀጥዬ ቢዘገይም ስለወሰዳችሁት ተገቢ ርምጃ ድሮም ዛሬም በሚገፉት ገባሮች ስም ምስጋና አቀርባለሁ ::
ከላይ ልብ በሚነካ ያመሰገኑ ሞንሟናና እምቢ ለጥላቻ መሰል ጥቂት ጨዋ ዋርካዊያን ተሳታፊዎችን በገባሮቹ ስም አመሰግናለሁ ::ከሰው በታች ተቆጥረን ለነበር ዋርካ ድንቅ መተንፈሻ መሆኗን ለመግለጽ እወዳለሁ ::ዛሬም ዋርካ ላይ የገባሮቹን ኒክ ያደረጉ ሁሉ የኛ እንዳልሆኑ እንዲታወቅና በ 21ኛው ክፍለ ዘመን ጋላ ጉዴላ መናፍቅ እያሉ በክፉ ቃል እምነታችንና ዘራችን በሚዘልፉ ላይ ርምጃው እንዲቀጥል አደራ እላለሁ ::
አክባሪያችሁ ከተፈለገ በሴኩሪቲ ሊያገለግላችሁ የሚወድ ዲጎኔ ሞረቴው ከአረንጉዋዴው አልማዝ ቡና መገኛ ከፊቾ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
በይሉል Joined: 16 Sep 2004 Posts: 1115 Location: Beylul-60km North of Assab.
Posted: Fri Feb 17, 2012 8:44 am Post subject:
የተከበሩ የዋርካ አስተዳዳሪ !!!!
እነዚህ ዋርካን የሚያቆሽሹ ሰወች
1.ሻእብያኒስታኖች
2.ወያኒስታኖች
3.ኦነጊስታኖች ናቸው .ከዚህ ቀደም በሌላ የብእር ስም እና በሌላ አጀንዳ ላይ አናት አናታቸዉን ተብለው የፈረጠጡ እና መግቢያ ቀዳዳ አጥተው ምድረ -በዳ የሚንከላወሱ መሆናቸዉን አሳምሬ አውቃለሁ .
ዛሬ ሻእብያ -ነገ ወያኔ -ከነገወዲያ ኦነግ በመሆን የሚሸረሙጡ ስለሆነ ለጊዜው የተሳካላቸው ይመስላቸዋል .እኛንም ያተራመሱ ይመስላቸዋል .
ሀያልነታቸው እና አስደንጋጪነታቸው በሚጠቀሙበት የአማርኛ ቃል ጠጣርነት እንጂ በፍሬዉና በጪብጡ አይደለም . በሀይማኖቱ ጠበቅ ያለ ክርክር ቢጀመር እንደለመዱት ይፈረጥጣሉ እንጂ ቆመው በጽናት አይከራከሩም .ይህ የፕሮፓጋንዲስቶች ታላቁ ቺሎታ ነው !!!
ማስደንገጥ እና ሰርፕራይዝ ማድረግ !!!ቢከፍቱት ተልባ !!!
ሀገራችንን ረግጠው የሚገዙ ወያኔወች እና እኛም ተራችን ደርሶዋል እነገዛችሁዋለን የሚሉን ጠባቦች ሰላማዊ እና ጨዋ ዉይይትን ለማደፍረስ እነዚህን ተላላኪወች እና ቆረቆንዳወች እየላኩ ሊያተራምሱን ሞክረዋል .ግን አይሳካላቸዉም .
እነስልኪ በሚከፍቱት አጀንዳ ከዚህ መድረክ ላይ እየተደቆሱ እና ቂጣቸዉን እየተገረፉ በራሳቸዉ ጊዜ እንደፈረጠጡ ሁሉ እነ trueobserver የሚባሉ ቅንዳሻም ሻእብያኖችም ድራሻቸው ጠፍቶዋል .ይህ የታሪክ ሂደት ስለሆነ ምንም የሚያደርጉት ነገር የለም .
አሁን እኔ የምጠይቅወት ሲሶ መንግስትዎን ያካፍሉን . ይህ ምን ማለት ነው ?ለሞደሬተርነት ሶስት ሰው ከመደቡ አንዱ እኛ ከእዚህ በቀጥታ የምንመርጠው -የምናዉቀው ሰው ይሁንልን .ሲሶ ያልኩት አንድ ሶስተኛዉን ስልጣን ለእኛ ካስረከቡን እኛ የምናምንበት እና እኛ ጋር እዚህ በየቀኑ የምናገኘው ከሶስቱ አንዱ ሆኖ ያገለግላል ማለት ነው .ስለዚህ ስልጣንዎን ያካፍሉን ..በተጨማሪም በቅጥታ ሪፖርት በማድረጉም እንሳተፋለን .
ከሰላምታ ጋር ..አክባሪዎ
በይሉል ---ሲሶ ስልጣን ጠያቂው !!!!! _________________ *The hardest thing about any political campain is how to win without proving that you are unworthy of winning!! E.stevenson
*Even if you win the rat race,you are still a rat!!!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ዘመድኩን Joined: 16 Nov 2004 Posts: 2370 Location: united states
Posted: Fri Feb 17, 2012 1:33 pm Post subject: Re: የተከበራቹሁ የዋርካ ታዳሚዎች
CyberEthiopia እንደጻፈ(ች)ው : ውድ የዋርካ ተሳታፊዎች፦
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዋርካ ጀነራል ላይ በጥቂት ግለሰቦች በተለይም ሀይማኖትን የሚመለከቱ አስጸያፊ እና ያልተገቡ መጻጽፎች የዋርካን ህግ እና ስርዐት የጣሱ ሆነው ስላገኘናቸው አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።
ስለሆነም ውድ የዋርካ ተሳታፊዎቻችን የየትኛውንም ሀይማኖት የሚያጎድፉ ፣ያልተገቡና አስጸያፊ ጹሁፎችን ሪፖርትን እንድታደርጎ ስንል የተለመደውን ትብብራችሁን እንጠይቃለን።
የሳይበርኢትዮጵያ አስተዳደር
የተከበሩ አድሚን ሼክ ሁሴን ጋዲ በመጀመሪያ የተከረ ሰላምታዬ ይደረሶት በመቀጠልም አረ ለመሆኑ እርሶ ከመጀመሪያው እምነታችን በዋልጌ እስላሞች ሲሰደብ አላስተዋሉም ነበር ? ሪፖርት የሚናረገውን ቅጥ ያጣ ንግግርስ ለምን ተንተርሰውት ከረሙ ?
ለማንኛውም እኔም በበኩሌ ለዚህ ቤት ሰላማዊ ውይይት የራሴን እንዳበረክት አሁንም በስሜ እየገቡ የሚሳደቡትን የአረብ ቡችሎች ከስር ከስሩ እየመነጠሩ ያስታግሱልኝ :: ይህ የማይደረግ ከሆነ ግን ሰው ነኝና ምላሽ መስጠቴ የማይቀር መሆኑን ይገንዘቡልኝ ::
ዘመድኩን ብቸኛውም ስሜ ሆኖ እንደሚቀጥልም ዋርካዊያን በሙሉ እንዲረዱል እፈልጋለሁ ::
ማሳሰቢያ ለመናፊቁ ዲጎኔ
አጋጣሚ አገኘሁ ብለህ ተገቢ ወዳልሆነ ውስለታ ከመግባት ተቆጠብ !
ወያኔው ዘመድኩን _________________ ሮሜ 1:16 በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና ።
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ቅመማቅመም Joined: 22 Jan 2008 Posts: 376
Posted: Fri Feb 17, 2012 3:12 pm Post subject: Re: የተከበራቹሁ የዋርካ ታዳሚዎች
ውድ የዋርካ አስተዳዳሪዎች ; ልባዊ ምስጋናዬን የማቀርብላቺሁ ከጥልቅ ሀዘን ጋር ነው ; ይህ ኢትዮጵያዊያን በመልካም ምግባር እንዲወያዩ አስባቺሁ የከፈታቺሁት መወያያ ቦታ በጥቂት ግለሰቦች በእጂጉ ተበላሸ ;
የስንቶቻቺን መንፈስና ልቦና ቆሰለ !!
ስለሀይማኖት ለማየት የሚሰቀጥጡ ለመስማት እጂግ የሚከብዱ አጸያፊ ነገሮች በዚህ በዋርካ ተጻፉ ; ብዙዎቻቺን አለቀስን ; ይህ ውሸት አይደለም !!!!!!!!!!!!! አልቅሰናል !!!!!! ኢትዮጵያዊያን እውን እንዲህ ነውረኞች ሆነናል ማለት ነው ?????????????
ሀይማኖቶችን የመስደብና የማዋረድ ተግባር ከከባድ ወንጀል አይተናነስም ; ይህን የሚያደርጉ ግለሰቦች ግጭትና ሽብር ለመፍጠር የሚሞክሩ ናቸውና በሕግ ሊጠየቁ ይገባል ; የማይታወቁ መስሏቸው የሽብር ስራቸውን ቢቀጥሉም እድሜ ለዘመኑ ቴክኖሎጂ ከየት አገር ብቻ ሳይሆን ከየት ቤት ሆነው ወንጀላቸውን እንደሚያከናውኑ ለማወቅ እጂግ በጣም ቀላል ነው ; ግን እዚህ ዋርካ ላይ በዋርካ አባላት ላይ የፈጸሙብን ግፍና በደል እጂግ ከባድ ነው ;
ያለምንም የሀላፊነት ስሜት እዚህ ዋርካ ላይ ሀይማኖቶችን ሲሳደቡና ሲያዋርዱ የነበሩትን ሁሉ ወደፊትም የሚያስቡትንም ጭምር እዚህ የሚለቀልቁት ክፉ ቃል እሳት ሆኖ ይፍጃቸው ; ያቃጥላቸው ;
ገሀነምን እዚሁ ከምድር ሆነው ናፍቀውታልና እንደነዚህ አይነቶቹን ከይሲዎች የራሳቸው አጸያፊ ቃላቶች በዚሁ በምድር እያሉ እሳት ሆነው ይብሏቸው ያቃጥሏቸው ; የኢትዮጵያ አምላክ ይሄን ሁሉ ይመለከታል ; ከባድ ፍርድም ይጠብቃቸዋል ; ወዮ የሚሉበት ቀን ቅርብ ነው !!!!!!
ይቅር ይበላቸው !!!!!!!!!!
ዋርካን ላለመጎብኘት ከራሴ ጋር ስሟገት ነው ጥሩ መልክታቺሁን ያገኘሁ ; ተባረኩ !!!!!!!!!!!
ስራው ብዙ እንደሆን አቃለሁ ግን እንደዚያ አይነቶቹን ክፉ መልክቶች ላንዲት ቀን ዋርካ ላይ አታሳድሩ አደራ !!!!!!!!!!!
እህታቺሁ ቅመሜ
CyberEthiopia እንደጻፈ(ች)ው : ውድ የዋርካ ተሳታፊዎች፦
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዋርካ ጀነራል ላይ በጥቂት ግለሰቦች በተለይም ሀይማኖትን የሚመለከቱ አስጸያፊ እና ያልተገቡ መጻጽፎች የዋርካን ህግ እና ስርዐት የጣሱ ሆነው ስላገኘናቸው አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።
ስለሆነም ውድ የዋርካ ተሳታፊዎቻችን የየትኛውንም ሀይማኖት የሚያጎድፉ ፣ያልተገቡና አስጸያፊ ጹሁፎችን ሪፖርትን እንድታደርጎ ስንል የተለመደውን ትብብራችሁን እንጠይቃለን።
የሳይበርኢትዮጵያ አስተዳደር
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
SAY-NO-TO-HATRED Joined: 12 Mar 2005 Posts: 1339 Location: united states
Posted: Fri Feb 17, 2012 8:11 pm Post subject:
ናፖሊዮን ዳኘ እንደጻፈ(ች)ው : ምንም ነገር ላይ ስትጽፊ የምታሳይው ኢትዮጵያዊነት መንፈስ እና ፈሪሀ እግዚያብሄት ህሌም ያስደምመኛል ::
በጣም የተከበርሽ ኢትዮጵያዊ ነሽ ! ቅን የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ ታስታውሺኛለሽ ::
ረዥም እድሜ !
ናፖሊዮን ዳኘ ::
SAY-NO-TO-HATRED እንደጻፈ(ች)ው : ውድ :ፈርሀ :እግዚአብሄር :ላላችሁ :ለዋርካ :አስተዳዳሪ :ወገኖቼ !...
ፈርሀ :እግዚአብሄር :ማሳየት :.....ድክመትና :...ድንቁርና :.....እንዳልሆነ :
አምናችሁበት :....ዋርካችን :...ፈርሀ :እግዚአብሄር :....እንዲኖራት :...
እርምጃ :ስለወስዳችሁ :.......እሱ :ፈጣሪ :....ሁሌም :ይለመናችሁ !....
ዋርካችን :ፈርሀ :እግዚአብሄርና :...ሞራል :የሰፈነባት :....ለማድረግ :
ጊዜ :....ጉልበትና :....ትእግስት :እንደሚጠይቅ :አንዳችንም :.....
አንጠራጠርም ::........ሰለዚህም :የሚሻለው :....በሌላው :አምድ :ስር :...
በአንድ :ወገኔ :እንደተጠቀሰው :....አንድ :ቁዋሚ :የሆነ :....አምድ :
ከፍቶ :....ክፉ :ጽሁፎች :....ሪፖርት :የሚደረጉበትና :....ከዛም :....እናንተ :..
ሁሉን :ከማንበብ :ይልቅ :....ያንን :የተለየ :...አምድ :በመጠቀም :ብቻ :..
......ዋርካችንን :ለማጽዳት :ይቀላል :....ብሎ :የጠቀሰውን :ወንድማችንን :...
ምክር :መጠቀም :.....እጅግ :ይጠቅማል :ብዬ :አምናለሁ ::...
......ውድ :የዋርካ :አድሚኖች :......ለምሳሌ :.....ተሳዳቢ :የብእር :ስሞች :
ብቻ :ሳይሆኑ :...ክፉ :የሀይማኖት :ጦርነት :...እያደረጉ :ያሉት :....ጥሩ :ስሞችን :...ተይዞም :.....አላህንና :ክርስቶስን :...
....ወዘተ :.....እየሰደቡ :ያሉ :....እንዳሉም :....ተረዱም ::.....ለዛ :ነው :..
......"መሰረዝ :የሚገባቸው :አምዶች :ሪፖርት :ማድረጊያ "....የሚል :
ቁዋሚ :ስቲኪ :አምድ :....ቢከፈት :....ሁሉን :ነገር :ያቀላል :ብዬ :...
አንድ :ወገኔ :ከእኔ :በፊት :ያቀረበውን :.......ግሩም :ሀሳብ :....ተቀበሉት :
በማለት :.....በትህትና :እለምናለሁ ::......
ዘወትር :አክባሪ :እህታችሁ :.....
እምቢ :ለጥላቻ
ነኝ ..........
========================
ውድ :ወንድሜ :ናፖሊዮን :.......ጽሁፋቸው :በፍጹም :ኢትዮጲያዊነትና :በጨዋነት :....
የተላበሰ :...በመሆኑ :ሳልታክት :ከምከታተላቸው :....ወገኖቼ :መሀል :
አንተ :አንደኛው :መሆኑን :....ላሳውቅህ :እወዳለሁ ::......በርታልኝ !
መልካምነት :ለራስ :ጤንነት :ነው ::.......እሱ :የጥንቱ :የኢትዮጲያ :አምላክ :
ምኞትህን :ሁሉ :ያሳካልህ !...
ወንድሞቼ :ተድላ :ሀይሉ :ዲጎኔ :እንዲሁም :ሁላችሁም :...ለዋርካ :
ንጽህና :..ድምጻችሁን :ያሰማችሁ :ሁሉ :.....የመልካም :ሁሉ :ምንጭ :..
ፈጣሪ :ምኞታችሁን :ሁሉ :ያሳካላችሁ ::........
ዘወትር :አክባሪ :እህታችሁ :
እምቢ :ለጥላቻ
ነኝ ......... _________________ WE ARE NOW AMBASSADORS FOR OUR BELOVED COUNTRY AND ONE DAY WE WILL BE CITIZENS IN ETHIOPIA, ONCE AGAIN!!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ክቡራን Joined: 04 Mar 2008 Posts: 4255
Posted: Fri Feb 17, 2012 9:03 pm Post subject:
ጠይና ይስጥልኝ ውድ የዋርካ አስተዳዳሪ :: አብዛኛው አስተያየት በተሳታፊዎች ስለተነገረ የኔ አስተያየት ምናልባት የሌሎችን መድገም ይሆናል ብዬ በማሰብ ከማንበብ ውጭ አስተያየት አልሰጠሁም ነበር :: በቅድሚያ ለዋርካ አስተዳደር ና ባለቤቶች ይሄንን የመሰለ ድህረ ገጽ በራሳችሁ ወጭና ጊዜ እንዲሁም ጉልበት ከፍታችሁ እንድንገለገልበትና ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሪጋርድለስ ኦፍ አወር ፖሎቲካል ኦፒኒየን ሀሳባችንን እንድናካፍል ስላደረጋችሁን አመሰግናችኌለሁ :: እናንተ ጋ ያለው ሀሳብን በነጻነት የመጻፍና የመግለጽ መብት ሌሎች የመንግስትም ሆነ የተቃዋሚ ሳይቶች ላይ ብናይ ምንኛ በወደድን በነበረ !! እናንተ ጋ ያለው ሀሳብን ያለ ገደብ የማንሸራሸር መብት ባልስልጣኖቻችን ላይም ብናይ ምናለ በተደስተን በነበረ !! ባጭሩ ዋርካ የመናገርና የመጻፍ መብታችንን ያስከበረች በመሆኗ እኔ ዋርካ ከምላት የዲሞክራሲ አምባ ብላት እመርጣለሁ :: ፌስ ሊፍቲንግ አይደለም እውነቴን ነው :: እናንተም ለማንም ሳትወግኑ ና ሳትቦድኑ አመለካከታችንን በእኩልነትና በቀናነት ስለምታስተናግዱ ለሌሎች የሰጣችሁት ትምህርት ና የምትሠጡት ትምህርት ቀላል አይደለም :: ለዚህ ማስረጃው የጎብኚዎቻችሁ ብዛት ነው :: እሳት የሆኑ ርዕሶች የሚወርዱበትና የሚገኙት እዚህ ነው :: በነገራችን ላይ እንደኛ የብእር ስም አውጥቶ ከሚሳተፈው ተሳታፊ በላይ ዋርካ በመላው አለም እጅግ ቡዙ አንባቢ ኢትዮጵያውያን አሏት :: ኢትዮጱያ የሁላችንም የጋራ ቤታችን ብትሆንም አስተሳሰባችን ግን ሊለያይ ይችል ይሆናል :: የናንተን አስተሳሰብ ና እመለካከት አልተከተለም ብላችሁ ያገላላችሁት አንድም ሰው የለም :: ተሳዳቢዎችንና የሰው እምነትን የሚዘልፉትን እያደናችሁ መያዛችሁ ተገቢ ውሳኔ ነው :: አንድ ሰሞን አናንተ ዝም ያላችሁ ስለመሰለን በነ አቶ ተደላ አስተባባሪነት አፈርሳታ ጀምረን ነበር :: አሁን ግን ዋጋቸውን ስለሰጣቸኌቸው ተመስገን ነው :: አገር የጋራችን ሀይማኖት ደሞ የግል ውሳኔአችን ነው :: በጉልበት ኢምፖስ የሚደረግ ሀይማኖት የለም :: እጅ መጠምዘዝና ማስገደድ ከተጀመረ የሀይማኖት ተቌም ሳይሆን የፖሎቲካ ድርጅት ሆኗል ማለት ነው :: ዋናው አስተያየት ልሰጥበት ያሰብኩት ጉዳይ ግን አንድ ሰው የጻፈውን በማየቴ ነው :: ከናንተ ፕሪንስፒል ውጭ በራሱ ስሜት ካታጎራይዝ ያደረገውን ነገር አነብብኩ :: .ይሄም ብቻ ሳይሆን ስልጣን አካፍሉኝ 1/3 ተኛውን ሲልም ሰማሁት :: የኔ ምክር ምንድነው ምንም አይነት ስልጣን እንዳታካፍሉ ነው :: እርዳታ ሊያስፈልጋችሁ ይችላል ያንንም አብዛኛው የዋርካ ተሳታፊ እንዳየሁት እኔንም በመጨመር ልንረዳችሁ ፍቃደኛ ነን :: አንድ ሰው ወይም ሁለት ሰው በቂም በቀል ወይም በቅናት ተነሳስቶ ሪፖርት የሚያደርገውን ሳይሆን አብዛኛው ጄኑዩን የሆነ ተሳታፊ ሪፖርት ያደረገውን አይታችሁ የራሳችሁን ውሳኔ መወሰን ትችላላችሁ :: ይሄ ጥሩና ፍትሀዊ አሰራር ይመስለኛል :: በተረፈ ሁሌም በዋርካ የዲሞክራሲ አምባ እውነተኛዎቹ የምዬ ኢትዮጵያ ልጆች እየኮሩባችሁና እያስታወሷችሁ ይኖራሉ :: እጊዘብሄር ጤናን ሰላምን እንዲሰጣችሁ ከልብ እመኛለሁ ::
በታላቅ አክብሮት :: ክቡራን :: _________________http://www.ethiopianthisweek.com
http://www.ethioonutube.com
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator