View previous topic :: View next topic
Author
Message
ደብረብርሀን 33 Joined: 17 Aug 2011 Posts: 252
Posted: Tue Mar 06, 2012 1:23 am Post subject: እሪ በል ጎንደር !!
ሰላም ወገኖች ,
በቁርጠኛው የወያኔ ተቃዎሚና : የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ በአቶ ኤልያስ ክፍሌ ዌብሳይት : ጥሩ ቀስቃሽ ጽሑፍ በአቶ ነጋ አንዳርጌ "" እሪ በል ጎንደር "" በሚል ርዕስ በተለይ ለጎንደር ሕዝብ ጥሩ ጽሑፍ ተጽፎል ::
http://www.ethiopianreview.com/amharic/?p=50000
ይህ ጽሑፍ ለጎንደር ሕዝብ በተለይ የቀረበ ቢሆንም : ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን /ኢሕአዴግ ጭቆና : በቃኝ እንዲል የቀረበ ነው በርግጥ የጎንደር ሕዝብ ከሁሉም በባሰ መንገድ : የሚደርስበት አፈና , ጭቆና እና ድርብ ድርብርብ አድሎ ከሁሉም በላይ የከፋ ስለሆነ ግንባር ቀደም ሆኖ ይህን ግፍ አሻፈረኝ ብሎ መነሳት ይኖርበታል :: የአቶ ነጋ አንዳርጌ መልእክትም ይህ ነው :: ከሁሉም ደስ ያለችኝ መቋጫ ግጥም ግን .....""ቀናኢ ነው ሲሉ ሰምቼ ነበረ :
አልቀና አለ ምነው ጎንደር ተቸገረ :
ምን ይስማው የሆን አባደፋር አዴ :
ትግሬ ሆነ ቢሉት ወልቃይት ጠገዴ ""... ይምትለው ግጥም ነች :: ቆንጆ ቀስቃሽ ጽሑፍ ነው : ግን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ነው ወያኔ /ኢሕአዴግ በሚገባው ቋንቋ ማነጋገር ለነገ ይደር የማይባል ነው ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እንድሪያስ Joined: 19 Mar 2004 Posts: 2120 Location: *****
Posted: Tue Mar 06, 2012 12:05 pm Post subject: Re: እሪ በል ጎንደር !!
ደብረብርሀን 33 እንደጻፈ(ች)ው : ሰላም ወገኖች ,
በቁርጠኛው የወያኔ ተቃዎሚና : የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ በአቶ ኤልያስ ክፍሌ ዌብሳይት : ጥሩ ቀስቃሽ ጽሑፍ በአቶ ነጋ አንዳርጌ "" እሪ በል ጎንደር "" በሚል ርዕስ በተለይ ለጎንደር ሕዝብ ጥሩ ጽሑፍ ተጽፎል ::
http://www.ethiopianreview.com/amharic/?p=50000
ይህ ጽሑፍ ለጎንደር ሕዝብ በተለይ የቀረበ ቢሆንም : ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን /ኢሕአዴግ ጭቆና : በቃኝ እንዲል የቀረበ ነው በርግጥ የጎንደር ሕዝብ ከሁሉም በባሰ መንገድ : የሚደርስበት አፈና , ጭቆና እና ድርብ ድርብርብ አድሎ ከሁሉም በላይ የከፋ ስለሆነ ግንባር ቀደም ሆኖ ይህን ግፍ አሻፈረኝ ብሎ መነሳት ይኖርበታል :: የአቶ ነጋ አንዳርጌ መልእክትም ይህ ነው :: ከሁሉም ደስ ያለችኝ መቋጫ ግጥም ግን .....""ቀናኢ ነው ሲሉ ሰምቼ ነበረ :
አልቀና አለ ምነው ጎንደር ተቸገረ :
ምን ይስማው የሆን አባደፋር አዴ :
ትግሬ ሆነ ቢሉት ወልቃይት ጠገዴ ""... ይምትለው ግጥም ነች :: ቆንጆ ቀስቃሽ ጽሑፍ ነው : ግን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ነው ወያኔ /ኢሕአዴግ በሚገባው ቋንቋ ማነጋገር ለነገ ይደር የማይባል ነው ::
አለም ቲያትር ናት - ያለው ማን ነበር ቅቅቅቅቅቅቅ ኤሊያስ ክፍሌ 'የሻቢያ ኤጀንት ......የኢትዮጵያ አውራ ጠላትና የጥፋት መልዕክተኛ ' ይባል ነበር እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ :: ዛሬ "የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ " ተባለ :: ገና ከጅምሩ ወያኔን መታገል አሁን ነው :: አንድ እንሁን ...እንተባበር ...እንደጋገፍ በሚልበት ወቅት የሻቢያና የወያኔ ኤጀንት ነው .....ኤርትራዊ ነው እያለ የሚያቀርበውን ጥሪ ሁሉ ውድቅ ለማድረግ ይሯሯጥ የነበረው ሁሉ ዛሬ ኤሊያስ የእምዬ ኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው - ይላል :: ነጋ አንዳርጌም ከነዚህ ሳሙናዎችና የድል አጥቢያ አርበኞች አንዱ እንደሚሆን ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም :: የድል አጥቢያ አርበኞች የምላቸው እኔ ድሮ የወያኔ ዕቃ የነበሩትንና አሁን ለውጥ በራሱ ጊዜ ይከሰታል ....መለስም በቅርቡ ይሄዳል ብለው በተስፋና በጉጉት የሚጠባብቁትንም ጭምር ነው :: ለምሳሌ አንዳርጋቸው ጽጌ ......ብርሀኑ ነጋ ...ብርቱካን ሚደቅሳ ........ፍስሀ እሸቱ .....መስፍን ነጋሽ ......ዳዊት ከበደ .....ተኮላ ሀጎስ .....አማረ አረጋዊ ....ወዘተ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ቢተወደድ Joined: 21 Jul 2009 Posts: 1501 Location: Dabra Za`Yet
Posted: Tue Mar 06, 2012 4:21 pm Post subject: Re: እሪ በል ጎንደር !!
ማሞ የሻቢያ የቁርጥ ቀን ልጅ ማለትህ ይሆን ? ነገሮች አይብዳዱብህ ::
ደብረብርሀን 33"]
ሰላም ወገኖች ,
Quote: የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ በአቶ ኤልያስ ክፍሌ
_________________ When we do it right No-one remembers,
When we do it wrong No-one forgets.
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እምቢ ለሀገር Joined: 13 Feb 2012 Posts: 258
Posted: Tue Mar 06, 2012 8:43 pm Post subject:
ሰላም ወንድሜ ደብረብርሀን 33 ስለ ሊንኩ አመሰገናለሁ
የጐንደር ህዝብ ባለፉት 20 አመታት ውስጥ ይኽ ነው የማይባል ግፍ እና በደል በወያኔዎቹ ደርሶበታል እስኪ ጥቂቶችን ልጥቀስልህ :-
1=በ 1985 ዓ .ም አባ አምሀ እየሱስ የተባሉ ባህታዊ ወጣቱን ሰብስበው ት /ተ ሀይማኖት ማስተማር ይጀምራሉ ::በት /ታቸውም ብዙ ወጣቶችን መሳብ ቻሉ ::ቀስ እያሉ ወጣቶችን በፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ላይ እንዲነሱ በዘዴ አነሳሱአቸው ::በዚህም ምክንያት ግጭት ተፈጠረ ;; ግጭቱን በሰላም መፍታት እየተቻለ ወያኔወች ብዙ ወጣቶችን በመትረይስ አጋደሙአቸው ::አስታውሳለሁ ጸጉራቸውን ድሬድ ያደረጉ (የጐንደር ህዝብ በተለምዶ ደደቢቶች ይላቸዋል ) ወታደሮች ፋሲል ግንብ አናት ላይ ሆነው አደባባይ እየሱስ ቤ /ክ ግቢ ውስጥ ተሰበሰበው የነበሩትን ወጣቶች በመትረይስ ጨፈጨፏቸው ::ግቢው የከብት ቄራ አስመሰሉት :: አንዲት የሰፈራችን ቆንጆ ኮረዳ አባቷ ሳር እየሸጠ ያሳደጋት ጡቷ ላይ በመትረይስ ተመታ ሙታለች :: አሁን ላይ ሁኘ ሳስበው በአባ አምሀ እየሱስ ዋና ገጸ ባህሪነት በወያኔ ጽሀፊ -ተውኔትነት የተዘጋጀ ቲያትር ነበር ::የጐንደር ህዝብን ሞራል ለማንኮላሸት የተዘጋጀ ሰርቶ -ማሳያ ትንፍሽ ብትሉ ....
2=ወያኔ ከገባ ጀምሮ ለጐንደር ከተማ የፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ሁኖ ለብዙ ዓመታት ባገለገለው አቶ ስዩም በተባለ ሰው አዛዥነት የብዙ ወጣቶች ሂዎት ተቀጥፏል ::ወጣቶች በሰላም እየተዝናኑ ባሉበት ደንገት በፈጥኖ ደራሽ ፖሊሶች ታፍነው ወደ ጎሀ ተራራ በመወሰድ ከፍተኛ ድብደባ ይካሄድባቸዋል ::ከድብደባው አይነት አንዱ :- ሁለት እጆችህን ለፍጥኝ ካሰሩህ በኍላ የክላሻቸውን ዘንግ ከገመዱ ማህል በመክተተት ያሽከረክሩታል ::ያኔ እጅህ ከደረትህ ሊገነጠል ይደርሳል :: የጎንደር ወጣቶችን አግኝተህ የእጅ ጡንቻቸውን ብታየው (በተለይ የፋሲል ሆቴል ሰፈር ልጆችን ) ጥቁር ክብ ንቅሳት መሳይ ነገር ታያለህ ::ወያኔ ለጐንደር ወጣቶች ያሰረው የጭቆና ጠባሳ ነው :: ይኽ ሁሉ ሲሆን ታድያ ፖሊሶች ሚጠይቁህ የደበቅከውን መሳርያ አውጣ እያሉ ነበር እንደዛ አስረው በባህር ዛፍ ዱላ ሚቀጠቅጡህ ::ከሰባበሩህ በኋላ ጥለሁህ ይሄዳሉ ::አንዳንዴም ማህል ከተማ ላይ በጥይት ደረትክን ብለው ይጥሉሀል ::ለምሳሌ አንድ ሲሳይ የሚባልን የአራዳ ሰፈርን ልጅ ከሚዝናናበት ናይት ክለብ አስውጥተው ከብሄራዊ ሎተሪ ፊት ለፊት አስፓልት ላይ : አስማማው (በቅጥል ስሙ አይረን ) በተባለ የድሮ ታጋይ ያሻውን አድራጊ ፖሊስ በክላሽ ደረቱን ተመቶ ሙቷል :: ባጠቅላይ ወጣቱ ወያኔን እንዲፈራ ብዙ ተቀጥቅጧል ::
እስኪ መጣሁ ....
እምቢ ለሀገር
ምንም ቢያደርጉን ኢትዮጵያዊነታችን ከማይጠፋው መንደር ጐንደር _________________ ETHIOPIA ETHIOPIA ETHIOPIA
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እምቢ ለሀገር Joined: 13 Feb 2012 Posts: 258
Posted: Tue Mar 06, 2012 9:44 pm Post subject:
3=በምሰረተ ልማት በኩል :- ቆንጆዎቹ ገና እንደገቡ ለጐንደር ከተማ ሰላቶው ጣልያን ጥሎላት የሄደውን ትልቅ የኤሌትሪክ ጄነሬተር ነቅለው ወደ ትግራይ ወስደዋል ::ስጋ ፋብሪካውን ለሸኹ በትንሽ ገንዘብ ጀባ ካሉት በኋላ ብዙ ሰውችን ከስራ በማፈናቀል ፋብሪካው የብዙ ዐመት የቦታ ግብርን ተሸክሞ ያንኮራፋል :: የጐንደር ከተማ እብርት ፒያሳ ልይ የሚገኘውን ቋራ ሆቴልን ለአዜብ ዘመዶች 3 ሚሊየን ብር በማይሞላ ተቀውሮላቸዋል ::ጥጥ መዳመጫም ተመሳሳይ እጣ ደርሶታል ! ዝነኛውን ጎሀ ሆቴልንም እንደዚሁ :: እንግዲህ ምን ቀረ እስኪ ቆንጆዎቹ የሰሩትን ልግለጽ :- ያች መከረኛ ዘመናዊ የገብስ ጠላ ማምረቻ ከ 200 ማይበልጡ ሰራተኞችን (ክድሪወችን ) የያዘች ዳሽን ቢራ
ሌላው ደግሞ የጐንደር ዩንቨርስቲ ማራኪና ቴዎድሮስ ካንፓሶችን አፍሮ ጽዮን በተባለ ትግራይ በቀል ኮንትራክተር ገንብተዋል ይኽንንም አባባ ጃንሆይ ናቸው ለመጀመሪያ ግዜ ማራኪ ብለው ሰይመው ለዩንቨርስቲ ግንባታ እንዲውል የፈቀዱት ::እንግዲህ ሌላ ምን ቀረ ....ኦ ! ሞት ይርሳኝ እረስቸ አንድ ዘመናዊ እስር ቤት እየተገነባ ነው በውጭ እስታንዳርድ በአፍሮ ጽዮን ኮንትራክተርነት ሌላው እንግዲህ ጥረኽ ግረኽ ብላ ነው :: እንድሜ ለመላኩ ተፈራ እሱ በቀይ ሽብር በትር ያባረራቸው የአሁኖቹ ዲያስፖራዎች የቤተሰባቸውን ጉሮሮ ይደፍናሉ መቸስ ሳይደግስ አይጣላ ነው ሚባለው
ይቀጥላል .............
እምቢ ለሀገር
አዲሱን እስር ቤት ሳይመርቅ ያመለጠው ጐንደሬው የእምዮ ኢትዮጵያ ልጅ _________________ ETHIOPIA ETHIOPIA ETHIOPIA
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ደብረብርሀን 33 Joined: 17 Aug 2011 Posts: 252
Posted: Wed Mar 07, 2012 12:13 am Post subject:
ሰላም ወንድሜ እምቢ ለሀገር ,
ስለሰጠኸው ዝርዝር ሀሳብ ከልብ አመሰግናለሁ እውነተኛ የአገሩ ሰው መሆንህና : ትክክለኛ የጎንደር ሕዝብ ተቋርቋሪነት እንዳለህ ምስክር የሚያሻህ አይደለም :: አንተ ከሰጠኸው የጎንደር ሕዝብ ሰቆቃ ትንሽ የምጨምረው ቢኖረኝም : እንደ በረከት ስምኦን አይነቶች "" ጥቁር አማራዎች "" ወይም ""ጥቁር ጎንደሬዎች "" ልበላቸው ይሆን ስለ ኤልያስ ክፍሌ ""የኢትዮጵያ የቀርጥ ቀን ልጅ "" ስለአልኩት ትንሽ መልስ ልስጣቸው ::
ኤልያስ ክፍሌ አሁን ባለው አቋምና እያደረገ ያለው ጸረ ወያኔ /ኢሕአዴግ ትግል : አይደለም የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ መባል ይቅርና ኒሻን ሽልማት ይገባዋል :: ፓለቲካ ትግልና የፓለቲካ ተክለ -ሰብነትም evolve የሚያደርግና በማያቋርጥ እድገት or it is in a constant metamorphosing sensate being ኤልያስ ክፍሌን የማውቀው : ቢያንስ አሜሪካ ከመጣሁ ወደ ሃያ አምስት አመት ይሆናል :: በነዚህ አመታት ካየሁት ትልቁ ነገር የማያወላወል ኢትዮጵያዊነት አቋሙና ጸረ -ወያኔነቱ ነው :: በርግጥ ከኤርትራ መንግሥት ጋር የነበረውን ግንኙነት ብዙዎቻችን አንደግፈውም ነበር :: ኤልያስ ይህን ግንኙነት ያደርግ የነበረው ለትግሉ ሲል መሆኑን ግልጽ ነው :: ውሎ አድሮ ግን ይህን ግንኙነቱን መፍረስ እንዳለበት መገነዘቡ ቀላል አይደለም :: እናም ከሻዕቢያ ሆነን ኢትዮጵያን ማዳን ከቶ እንደማይቻል አረጋግጦል :: ሻዕቢያ በታጋዮ ሕዝባችን ላይ በትሩን ሲያነሳ : ስሜቱ እና የነጠረ ኢትዮጵያዊነቱ እንደ እሳተ -ጎመራ ገንፍሎ ሲወጣ ሁላችንንም አስደስቶናል :: ይህ መቼም ለወያኔዎች ሊያስደስታቸው እንደማይችል የታወቀ ነው :: እንዲያውም እሱ በሚያደርገው የሳይበር ትግልና : በተጨባጭም አገር ቤት ላለው ትግል በሚያደርገው አስተዋጽኦ የወያኔ መንግሥት መሽበሩና : የውሽት የሽበርተኛ ክስ መመስረት ወያኔ የተሽበረ ለመሆኑ ማስረጃ ነው :: እና ኤልያስ ክፍሌ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ካልተባለ : ማን እንደሚባል ትፈልጋላችሁ ከወያኔ ጋር ሆዱን ለመሙላትና ለጥቅም ሲል ከመንግሥት ጋር የሚሞዳሞደውን ነው
የድል -አጥቢያ አረበኞች ብለህ ያልካቸው ሰዎች : አብዛኞችን እኛ ኢትዮጵያውያን የምናከብራቸው ስዎችና ታጋዮቻችን ናቸው ከድቅድቅ ጨለማ ለመውጣትና የኢትዮጵያን ዳግሚያ ትንሳኤ ለማምጣት የሚታገሉ ናቸው :: ስም ተዛብርቆብህ ይሁን በስህተት አንድ ሁለት የጨመርካቸው ሰዎች የናንተ ናቸውና : እዚያው ጠቅልላቸው እኛ አንፈልጋቸውም በተለይ የወያኔው የሪፓርተር አዘጋጅ አማረ አረጋዊን "" ሥጋ ጥራ ቢሉት ጣፊያ አመጣልኝ "" አሉ .......ሰው ጠርተህ ሞተሃል
እምቢ ለሀገር - የወያኔ /ኢሕአዴግ መንግሥት በጎንደር ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን : መጠነ -ሰፊ አፈና ጭቆና እናውቃለን :: በርግጥ አቶ ነጋ አንዳርጌ ያቀረበው ጽሑፍ : የጎንደር ምሁራንና ሊህቃን : በተለይ ውጭ ያሉትና አንጻራዊ ነጻነት ያላቸው ወገኖች ለምን ይህን ሀቅ ለአለም ለማጋለጥ አይሞክሩም ነው :: ይህ ምንም እንኳ ዝም ያለው አብዛኛው ኢትዮጵያውያን ምሁራን ቢሆንም : ጎንደሬው ካለው የቁጥር ብዛት አንጻር የሚጠበቀውን ያህል አልተደረገም :: አንዱ ሌላውን Blame መደራረጉን አይሁንና አብዛኛው ተኝቶል ከዚህ ከተገባው በጣም ውድቅት እንቅልፍ ከዚህ የበለጠ ወያኔ ምን ቢያደርግ ነው ከእንቅልፋችን የምንነቃው የጎንደር ሕዝብ በከፋ የወያኔ የዘር ጥላቻ ሰለባ ከሆነ ሀያ አመታት ሆኖል :: ከሁሉም የልማት እንቅስቃሴዎች ተቋዳሽ እንዳይሆን ወያኔ አግዶታል :: የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ለማሳየት እንደሞከረው ከሁሉም አካባቢዎችና ክ /ሀገሮች በጎንደር ምንም ልማት እንዳይካሔድ ከፍተኛ መመሪያ አለ ነው የሚለው :: ጣሊያን ስርቶት የሔደው እነዚያ ፒያሳ ያሉትም ሕንጻዎች ብቻ ቀርተዋል :: እነሱም አርጅተው ሊወድቁ አንድ ሳምንት የቀራቸው ናቸው :: የአጼ ፋሲል ግንብ እራሱ እድሳት እንክብካቤ ከማጣቱ የተነሳ አንድ ሀሙስ የቀረው የሚመስለው :: በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ከሰባ እና ሰማንያ NGO ድርጅቶች ጎንደር አይደሱም :: እነ አያሌው ጎበዜ / የአገው ተወላጁና : የወያኔ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይህ እንዳይሆን ይተገብራል :: እና ይህ ሁሉ እየሆነ : ያ ጀግና ሕዝብ እንዴት ዝም ብሎ ይተኛል አዎ በርግጥ በዚህ ሁሉ የወያኔ አፈና : እንደ ጥጋቤ አዲሴ ያሉ ብዙ የሚዋደቁም አሉ በርግጥ እንደዚህ አይነቱን ጀግና ቁጥራቸውን መጨመር አለብን :: የጽሑፉ ዋና መልዕክት ይህ ነው እንጂ ከጎንደር ወያኔዎች ያልወሰዱት ነገር የለም :: ያልወሰዱትን መቁጠር ይሻላል :: ወያኔዎች የዚህን ሕዝብ ጀግንነት በሚገባ ስለሚያውቁት : የሚጠቀሙት የቶርቸር ዘዴ ከሁሉም የከፋና Dehumanizing መሆኑ የታወቀ ነው :: ቢሆንም ዋናው ከዚህ የከፋ ስለማይመጣ ከመታገልና ከመነሳት የተሻለ አማራጭ የለም :: በርግጥ ለዚህ ድግሞ የሚያታግል ድርጅት ያስፈልጋል :: ይህ ሁላችንም የተረዳነው ስለሆነ : የሕዝባችንን የፍርሀት ድባብ ለመግፈፍ ድርጅት አስፈላጊ ነው :: ከዚያ ግን ወያኔ ያሳቡት የጸረ -ኢትዮጵያ ቅጀታቸው መትነኑ የማይቀርለና የዲያሊቲካዊ ሕግ ነው ::
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ
ሞት ለወያኔዎችና ለባንዳዎች
እምቢ ለሀገር እንደጻፈ(ች)ው : ሰላም ወንድሜ ደብረብርሀን 33 ስለ ሊንኩ አመሰገናለሁ
የጐንደር ህዝብ ባለፉት 20 አመታት ውስጥ ይኽ ነው የማይባል ግፍ እና በደል በወያኔዎቹ ደርሶበታል እስኪ ጥቂቶችን ልጥቀስልህ :-
1=በ 1985 ዓ .ም አባ አምሀ እየሱስ የተባሉ ባህታዊ ወጣቱን ሰብስበው ት /ተ ሀይማኖት ማስተማር ይጀምራሉ ::በት /ታቸውም ብዙ ወጣቶችን መሳብ ቻሉ ::ቀስ እያሉ ወጣቶችን በፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ላይ እንዲነሱ በዘዴ አነሳሱአቸው ::በዚህም ምክንያት ግጭት ተፈጠረ ;; ግጭቱን በሰላም መፍታት እየተቻለ ወያኔወች ብዙ ወጣቶችን በመትረይስ አጋደሙአቸው ::አስታውሳለሁ ጸጉራቸውን ድሬድ ያደረጉ (የጐንደር ህዝብ በተለምዶ ደደቢቶች ይላቸዋል ) ወታደሮች ፋሲል ግንብ አናት ላይ ሆነው አደባባይ እየሱስ ቤ /ክ ግቢ ውስጥ ተሰበሰበው የነበሩትን ወጣቶች በመትረይስ ጨፈጨፏቸው ::ግቢው የከብት ቄራ አስመሰሉት :: አንዲት የሰፈራችን ቆንጆ ኮረዳ አባቷ ሳር እየሸጠ ያሳደጋት ጡቷ ላይ በመትረይስ ተመታ ሙታለች :: አሁን ላይ ሁኘ ሳስበው በአባ አምሀ እየሱስ ዋና ገጸ ባህሪነት በወያኔ ጽሀፊ -ተውኔትነት የተዘጋጀ ቲያትር ነበር ::የጐንደር ህዝብን ሞራል ለማንኮላሸት የተዘጋጀ ሰርቶ -ማሳያ ትንፍሽ ብትሉ ....
2=ወያኔ ከገባ ጀምሮ ለጐንደር ከተማ የፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ሁኖ ለብዙ ዓመታት ባገለገለው አቶ ስዩም በተባለ ሰው አዛዥነት የብዙ ወጣቶች ሂዎት ተቀጥፏል ::ወጣቶች በሰላም እየተዝናኑ ባሉበት ደንገት በፈጥኖ ደራሽ ፖሊሶች ታፍነው ወደ ጎሀ ተራራ በመወሰድ ከፍተኛ ድብደባ ይካሄድባቸዋል ::ከድብደባው አይነት አንዱ :- ሁለት እጆችህን ለፍጥኝ ካሰሩህ በኍላ የክላሻቸውን ዘንግ ከገመዱ ማህል በመክተተት ያሽከረክሩታል ::ያኔ እጅህ ከደረትህ ሊገነጠል ይደርሳል :: የጎንደር ወጣቶችን አግኝተህ የእጅ ጡንቻቸውን ብታየው (በተለይ የፋሲል ሆቴል ሰፈር ልጆችን ) ጥቁር ክብ ንቅሳት መሳይ ነገር ታያለህ ::ወያኔ ለጐንደር ወጣቶች ያሰረው የጭቆና ጠባሳ ነው :: ይኽ ሁሉ ሲሆን ታድያ ፖሊሶች ሚጠይቁህ የደበቅከውን መሳርያ አውጣ እያሉ ነበር እንደዛ አስረው በባህር ዛፍ ዱላ ሚቀጠቅጡህ ::ከሰባበሩህ በኋላ ጥለሁህ ይሄዳሉ ::አንዳንዴም ማህል ከተማ ላይ በጥይት ደረትክን ብለው ይጥሉሀል ::ለምሳሌ አንድ ሲሳይ የሚባልን የአራዳ ሰፈርን ልጅ ከሚዝናናበት ናይት ክለብ አስውጥተው ከብሄራዊ ሎተሪ ፊት ለፊት አስፓልት ላይ : አስማማው (በቅጥል ስሙ አይረን ) በተባለ የድሮ ታጋይ ያሻውን አድራጊ ፖሊስ በክላሽ ደረቱን ተመቶ ሙቷል :: ባጠቅላይ ወጣቱ ወያኔን እንዲፈራ ብዙ ተቀጥቅጧል ::
እስኪ መጣሁ ....
እምቢ ለሀገር
ምንም ቢያደርጉን ኢትዮጵያዊነታችን ከማይጠፋው መንደር ጐንደር
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator