View previous topic :: View next topic
Author
Message
ዋናው Joined: 16 Dec 2003 Posts: 2633 Location: ሕልም ዓለም
Posted: Tue Apr 03, 2012 11:20 am Post subject: አስተያየት ስጡበት
ሠላም ውድ ዋርካዊያን /ያት
እዚህ ሰፈር ፖስት ጋደረግኩ ቆየው ልበል መጣፊያው ሁሉ አዲስ ሆነብኝ 'ኮ ... የሆነው ሆኖ ዛሬ አመጣጤ እቺን ቪዲዮ አይታችሁ አስተያየታችሁን ስጡበት ለማለት ነው ይህን ቪዲዮ የሠራው ሠው ኢሜይል ሰደደልኝና በዛውም የኔን ስክሪፕት ማለትም ድርሰት ለሆም ቪዲዮ ስለተጠቀመበት አመሰገነኝ ነገሩ በርግጥ ገርሞኛል ... እንዴ ብዬ ስራዎቼን ጉግል ውስጥ ገብቼ ስጎለጉል በርካቶቹ ብዙ ድረ -ገጾች ላይ ተለጥፈው አገኘዋቸው አትላንታና ሌሎች ከተማዎች ውስጥ የሚታተሙ ጋዜጣዎች ላይ መውጣታቸዉንም አየው ... በርግጥ ሕዝብ እንዲያነበው ነውና ድረ -ገፅ ላይ የጻፍኩት በርካታ ዓይኖች ስለጎበኙት እሰየው አልኩኝ ያገረመኝ ግን ሌላ ነው አዲሳባ የሚታተም አንድ የግል መፅሔት ላይ ምናልባት ታስታውሱት ይሆናል 'ከጨረቃ ስር ' የምትለዋን የቆየች ድርሰቴን ስሜን ገንጥለው ታሪኩን ትንሽ ቀይረው አወጡት የድርሰቱ ባለቤት በኩራት ስሙን ከድርሰቱ ራስጌ እና እግርጌ ለጥፎታል
በርግጥ አሁን ዘመኑ የዌብ 2.0 ነው ሁሉም ያለዉንም የሌለዉንም የፈጠረዉንም ያልፈጠረዉንም ሼር ለማድረግ የሚራወጥበት ዘመን ነው
የድርሰቴ እርዕስ ሸጥኳት ! ይሰኛል እቺን ይጫኑና ያግኟት የፊልሙ ባለቤት ሥራዉን ከአንድ ጋዜጣ ላይ እንዳገኘ ነግሮኛል ስሜን አድኖ እዚህ ምውደው ሰፈር ዋርካ ስር ስላገኘኝ ደስ ብሎኛል
ፊልሙን ለማየት እዚች ጋር ጠቅ ያድርጉ እኔ የራሴ በርካታ አስተያየቶች አሉኝ ቀድሜ መስጠቱ ትንሽ ግብዝነት እንዳያስመስልብኝ ብዬ ቀድሜ የናንተን አስተያየት መስማት ፈለግኩኝ
መልካም ቀን
_________________ ጥበብ ከእኔ የበለጠ ጠንካራ ናት እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን እሷ እንደፈለገችው ታደርገኛለች::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ተድላ ሀይሉ Joined: 17 Mar 2006 Posts: 4451 Location: ኢትዮጵያ
Posted: Tue Apr 03, 2012 9:28 pm Post subject: Re: አስተያየት ስጡበት
ዋናው እንደጻፈ(ች)ው : ሠላም ውድ ዋርካዊያን /ያት
እዚህ ሰፈር ፖስት ጋደረግኩ ቆየው ልበል መጣፊያው ሁሉ አዲስ ሆነብኝ 'ኮ ... የሆነው ሆኖ ዛሬ አመጣጤ እቺን ቪዲዮ አይታችሁ አስተያየታችሁን ስጡበት ለማለት ነው ይህን ቪዲዮ የሠራው ሠው ኢሜይል ሰደደልኝና በዛውም የኔን ስክሪፕት ማለትም ድርሰት ለሆም ቪዲዮ ስለተጠቀመበት አመሰገነኝ ነገሩ በርግጥ ገርሞኛል ... እንዴ ብዬ ስራዎቼን ጉግል ውስጥ ገብቼ ስጎለጉል በርካቶቹ ብዙ ድረ -ገጾች ላይ ተለጥፈው አገኘዋቸው አትላንታና ሌሎች ከተማዎች ውስጥ የሚታተሙ ጋዜጣዎች ላይ መውጣታቸዉንም አየው ... በርግጥ ሕዝብ እንዲያነበው ነውና ድረ -ገፅ ላይ የጻፍኩት በርካታ ዓይኖች ስለጎበኙት እሰየው አልኩኝ ያገረመኝ ግን ሌላ ነው አዲሳባ የሚታተም አንድ የግል መፅሔት ላይ ምናልባት ታስታውሱት ይሆናል 'ከጨረቃ ስር ' የምትለዋን የቆየች ድርሰቴን ስሜን ገንጥለው ታሪኩን ትንሽ ቀይረው አወጡት የድርሰቱ ባለቤት በኩራት ስሙን ከድርሰቱ ራስጌ እና እግርጌ ለጥፎታል
በርግጥ አሁን ዘመኑ የዌብ 2.0 ነው ሁሉም ያለዉንም የሌለዉንም የፈጠረዉንም ያልፈጠረዉንም ሼር ለማድረግ የሚራወጥበት ዘመን ነው
የድርሰቴ እርዕስ ሸጥኳት ! ይሰኛል እቺን ይጫኑና ያግኟት የፊልሙ ባለቤት ሥራዉን ከአንድ ጋዜጣ ላይ እንዳገኘ ነግሮኛል ስሜን አድኖ እዚህ ምውደው ሰፈር ዋርካ ስር ስላገኘኝ ደስ ብሎኛል
ፊልሙን ለማየት እዚች ጋር ጠቅ ያድርጉ እኔ የራሴ በርካታ አስተያየቶች አሉኝ ቀድሜ መስጠቱ ትንሽ ግብዝነት እንዳያስመስልብኝ ብዬ ቀድሜ የናንተን አስተያየት መስማት ፈለግኩኝ
መልካም ቀን
ሰላም ዋናው :-
'የቅጅ መብት ሣይጠብቁ የሌብነቱን ጉዳይ ':- ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ከማን የተማሩትን ሥራ ላይ ያውላሉ ብለህ ነው ውጭ አገር ያሉት ሥምህን ካላወጡትና የአንተንም ፈቃድ ካልጠየቁ በአድራሻቸው ጽፈህ በይፋ እንዲያርሙ ብታደርግ አይከፋም :: መነበቡ ብቻ ሣይሆን ሕግና ሥርዓት ባለበት ዓለም ውስጥ እየኖሩ አገር ቤት እንዳሉት ሌባ ባልደረቦቻቸው ያሻቸውን እንዲያደርጉ መፍቀድ የለብንም ::
በለጠፍከው አድራሻ ዩቲዩብ ላይ የተቀመጠውን የቪዲዮ ክሊፕ አየሁት :: የአንተ ጽሑፍ ዋና የማጠንጠኛ ኃሣብ አንድ ሰዓሊ ስለሣላት የአንዲት ሴት ሥዕልና ከሥዕሏ ጋር በምናቡ የፈጠረውን ትሥሥር የሚተርክ ነው :: ቪዲዮ ክሊፑ ላይ ግን ሁለት ዓይነት ምሥሎችን እናያለን :- የሥዕል ንድፍና የአንዲት ሴት ፎቶግራፍ :: ሁለቱ ምሥሎች እንዴት የአንተን ድርሰት ኃሣብ ሊገልጹ እንደተፈለገ አልገባኝም :: ምናልባት ሠዓሊው ያለቀለትን ሥዕል ከንድፍ እስከ ሙሉ ሥዕል ሲያጎለብት በዚያ ሂደት የተፈጠሩበትን የሥሜት ቁርኝት የሚያሣይ ተከታታይነት ያለው ቅንብር ቢሆን ትርጉም ሊሠጥ ይችል ነበር :: እንዲያውም ፎቶግራፉ ላይ የምትታየዋ ሴት እኮ የላሊበላ መስቀል በአንገቷ ላይ አላጠለቀችም :: በእኔ አስተያዬት የቪዲዮ ክሊፑ ሙሉ ሥራ ለመሆን ገና ብዙ ይቀረዋል :: ሙከራው ግን የሚበረታታ ነው ::
ተድላ _________________ የወያኔ ሕገ -አራዊት አንቀፅ 39 ኢትዮጵያን የመበታተኛ ፈንጂ ነው !
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
ተድላ ሀይሉ ዘብሔረ -ኢትዮጵያ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ፕላዞግ Joined: 06 Dec 2008 Posts: 31
Posted: Tue Apr 03, 2012 11:55 pm Post subject:
ዋናው ነገር የዋናው ስራ ተደብቆ አለመቅረቱ : ዞሮ ዞሮ መውጣቱ !! ድንቅ ፍልስፍና እና እይታ ነው ::
ከተቻለ ሌላ ክሊፕ አንተው ራስህ ሰርተህ ዩቲዩብ ላይ ብታስቀምጥ ይሄኛው በክብር ቢነሳ መልካም ይመስለናል :: የተከበሩ ሰዐሊው መንተባተብ : ተድላም ጠቆም እንዳረገው ከጭብጡ ጋር የማይሄድ ምስል ያውም 'ፎቶ ': ጭስ የሌለው ትምባሆ : ኤክስፕሬሽን የጎደለው ትረካ : ድምፅ እና ምስል ኤዲት ሳይደርግ ስናየው ለዚህ ምርጥ ስራ አይገባም ነበር ግን ሆነ ...ብለን ተቆጨን !!!
መካሰሱና መከሳከሱ ሌላ የጊዜና የሞራል ፍጆታ ይኖረዋል : ይሄ እንደማስጠንቀቅያ ቢወሰድ እና ያሉትን ነገሮች ሰብሰብ አድርጎ በጊዜ ወደኛ የዋንሽ ተደራሲያን ወርወር ለማድረግ ተፍ ተፍ ቢጀመርስ ? ተጀምሮም ከሆነ ትኩረት ቢሰጠውስ ? የፍርድ ሂደት ከምንከታተል የዋናውን በረከት ብንኮመኩምስ ...
በርታ ሲለጥቅም አትጥፋ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
-...- Joined: 09 Feb 2012 Posts: 312
Posted: Wed Apr 04, 2012 3:36 am Post subject:
አልሰሜን ግባ በለው አሉ :: ዋኒቾ ሙሉው ጥላአልባ ራሱ ተጠርዞ እየተሸጠ ነው :: ዝግችሎት ፈልገህ ጥላአልባን ግዛና መጨረሻውን ትወደው እንደሁ እይ :: አትላንታ የምታውቀው ሰው ካለ ፈልጉልኝ በላቸው :: መደምደሚያውን የጻፈው ጠራዡ ሌባ ነው :: _________________ እሰይ ተመስጌን አምላኬ ለካስ በክብርነቴ እራሴን ሆኜ እኔነቴን ፈልጌ አግኝቼዋለሁ !?
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እንሰት Joined: 30 Jan 2005 Posts: 1198 Location: united states
Posted: Thu Apr 05, 2012 8:05 am Post subject:
-...- እንደጻፈ(ች)ው : አልሰሜን ግባ በለው አሉ :: ዋኒቾ ሙሉው ጥላአልባ ራሱ ተጠርዞ እየተሸጠ ነው :: ዝግችሎት ፈልገህ ጥላአልባን ግዛና መጨረሻውን ትወደው እንደሁ እይ :: አትላንታ የምታውቀው ሰው ካለ ፈልጉልኝ በላቸው :: መደምደሚያውን የጻፈው ጠራዡ ሌባ ነው ::
መርዶ በቃ እንዲህ በአደባባይ ሆነ የሚነገረው :: ሰ .....ው ግን በቃ በጣም ብሶበታል ማለት ነው ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ተድላ ሀይሉ Joined: 17 Mar 2006 Posts: 4451 Location: ኢትዮጵያ
Posted: Fri Apr 06, 2012 8:32 pm Post subject:
እንሰት እንደጻፈ(ች)ው : -...- እንደጻፈ(ች)ው : አልሰሜን ግባ በለው አሉ :: ዋኒቾ ሙሉው ጥላአልባ ራሱ ተጠርዞ እየተሸጠ ነው :: ዝግችሎት ፈልገህ ጥላአልባን ግዛና መጨረሻውን ትወደው እንደሁ እይ :: አትላንታ የምታውቀው ሰው ካለ ፈልጉልኝ በላቸው :: መደምደሚያውን የጻፈው ጠራዡ ሌባ ነው ::
መርዶ በቃ እንዲህ በአደባባይ ሆነ የሚነገረው :: ሰ .....ው ግን በቃ በጣም ብሶበታል ማለት ነው ::
ወንድሜ እንሰት :-
"አገር ሲበላሽ ጓጉንቸር ያፈላል " ይባላል :: እና ዛዲያ የአገሪቱ የጥበብ ሰዎች በዘመናት ድካም ያወረሱንን ትውፊት የዘመኑ ሞጭላፊዎች እንደራሳቸው ሥራ እያደረጉ ሲነግዱበት የሚያስተውል ትውልድ ሥርቆት የዕርድና መለኪያ አድርጎ ተቀብሏል :: ይህ ድርጊት ሊቆም የሚችለው ከትንሿ ሌብነት ጀምሮ ያለውን ጥፋት መከላከል ስንጀምር ብቻ ነው ::
ተድላ _________________ የወያኔ ሕገ -አራዊት አንቀፅ 39 ኢትዮጵያን የመበታተኛ ፈንጂ ነው !
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
ተድላ ሀይሉ ዘብሔረ -ኢትዮጵያ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ዋናው Joined: 16 Dec 2003 Posts: 2633 Location: ሕልም ዓለም
Posted: Sat Apr 07, 2012 1:30 am Post subject:
ምን ጎርጓሪ ምን ያወጣል ነው 'ሚባለው ...
አያረጉትም አይባልም ድሮም የወደቀ ዛፍ መጥረቢያ እንደሚበዛበት ይታወቃል ... ደግነቱ እሩብ ሚልዮን ዕይታን ያፈራች ጥላ ዓልባ አባቷ ማን እንደሆነ አይታወቅም ቢባል አይታመንም እናም ደፍረው ቢያደርጉት 'ንኳን ዋርካዊያን /ያት ተደራሲዎቼ ከመፀሐፉ ግርጌ ያለዉን የሀሰት ስም ፍቀው የባለቤቱን ስም እንደሚፅፉበት ጥርጣሬው የለኝም :: (ድሮም ዓላማዬ ቸብችቦ ሳንቲም ከመቁጠር ምናቤን በማጋራት ከምወደው ወገኔ ጋር በሀሳብ መገናኘት ነውና )
ስለጥላ -ዓልባ ከተነሳ መቼም ከዚህ በፊት የተኛ ቤት እንደሆነ እንጃ 'ንጂ አውርቼው ነበር የመቋረጡ ምክኒያት መካከለኛው ምስራቅ የሚታተም አንድ አበሻዊ መፀሔት ላይ በተከታታይ ክፍሎች እየወጣ መሆኑን ሳታውቁት አትቀሩም :: መጀመሪያ ላይ ብዙም ተቃውሞ አልነበረኝም ዋርካን ገልጠው ማንበብ ለማይችሉ መዳረሱንም ወድጄው ነበር ኋላ ግን የዋርካ ወንድምና እሕቶቼንም ምክር ስሰማ እኔም ከ 300 በላ ገፆች ያሉትን ስራ ለመፃፍ ካፈሰስኩት ጊዜ አኳያ ሳስበው ለዛዉም በቅጡ ፈቃድ ሳልጠየቅ ዝም ብዬ እነሆ በረከቱን ማለቱ ወደጅልነት ያመራብኝ መሰለኝ ::
በርግጥ የድርሰቱ መግቢያ ላይ እንዲህ የሚል ፅሑፍ አስፍሬ ነበር ታዲያ ኮፒራይቱ በሣይበር ኢቲዮጲያ አላፊነት ቢሆንም አደራ በመተማመን ይሁን አዎ ሳይበር ኢትዮጵያዎች እንደምናውቀው ዋርካችን በትክክል ለመስራቱ ሳይታክቱ ከመጣር ውጪ ለማንም ለምንም ግድ የላቸዉም ዋናው የሚባል አንድ ባተሌ ስለመኖሩ ሁሉ ላያውቁ ይችላሉ ያም ሆነ ይህ መተማመኑ ከጠፋ ጥላ -ዓልባ ለጊዜው ጥላ ስር አረፍ ብትልስ ብዬ ከጓሮ ሸጎጥኳት ብዙዎቹ እንደሚያደርጉት ላጲስ ይዤም አልተመለስኩባትም ::
እኔም የመጻፉ ጥማት ስላለብኝ ካንባቢያኖቼ ጋር መገናኛ ይሆነኝ ዘንድ አጫጭር ልቦለዶች ብዬ መጻፌን ቀጠልኩኝ እየው ዛሬ ላይ ደርሼ ከዚህም ሰፈር መዘገን ተጀመረ :: በርግጥ እውነቱን ለመናገር አልከፋኝም ቢጣፍጥ ነው የተዘገነው ብዬ ደስ አለኝ ::
በዚህ አጋጣሚ መፃፍ የማቋረጤ ምክኒያት ከዚህ ጋር የተያያዘ እንዳልሆነ ተረዱልኝ ሕይወት ሁሌም አትደላም አንዳንዴ ለሱስ የሚተራርፉ ሽርፍራፊ ጊዜያትንም ትነጥቃለች ::
ወደ ቤቱ ርዕስ ልመለስ
ወንድሞቼ ፕላዞ እና ተድላ ለምክራችሁ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ አደርገው ዘንድም ብርታቱን እንዲሰጠኝ በፀሎታችሁ አትርሱኝ (ምን እናድርግ የዛሬ 8 እና 9 ዓመት ከዳሞት ቅኔ ቤት ሆነን እዚህ ዋርካ ስር ቋንቋን ስንማር ታላላቅ የዋርካ ፀሐፍት እና የቋንቋ ጠበብት የተፃፈ ሁሉ መፀሐፍ የተገጠመ ሁሉ መድብል አይሆንም ብለው ስላስተማሩ 'ኮ ነው : በዚህ ላይ ለሁሉም ጊዜ አለው ::
ሸጥኵት ወይም ወደፊልም የቀየረ ሰው እንዳለው ሠዓሊው የሚለው ስራ ስራዉን እኔ ባየዉበት ዕይታ ያየው አይመስለኝም ወይም የራሱን ቴክኒክ ተጠቅሞ ይሆናል የሰራው ግን ግን ፊደላቱን ስጋ አልብሶ ስላሳየኝ አመሰግነዋለሁ ... ስለፊልም ጥበብ አሁን ተማሪ ቤት ገብቼ እየተንደፋደፍኩበት ያለ ጉዳይ ስለሆነ ባሕሩ ጥልቅና ሰፊ መሆኑን ስለማውቅ እሱ የሰራዉን ማቅለሉ ይከብደኛል ደፍሮ ከጀመረው ደፍሮ እንደሚያሻሽለው ግን ተስፋ አለኝ ::
እዚህ አጭር ፊልም ውስጥ ብዙ ነገር ማካተት ይቻላል በርግጥ ከረጅም ፊልም አጭር ፊልም መስራት ይከብዳል አጭር ፊል ማለት በራሱ ግጥም እንደማለት ነው በትንሽ ዕይታዎችና ንግግር ብዙ መናገር መቻል ማለት ነው ዛሬ አንቱ የተባሉ የፊልም ዳይሬክተሮች የመጀመሪያ ሥራዎቻቸው አጫጭር ፊልሞችና ማስታወቂያዎች ናቸው
እነኚህ ዋና የፊልም ጥበብ ቅመሞች በደምብ ቢሠሩበትስ
Story
Diegesis
Plot
continuity
እና የመሳሰሉት
ገፀ -ባሕሪን ስለመላበስ ... እ .... በፊልም ርዕስ ከሆነ ምናወራው ቢቆየን ይሻላል ይህንንም ያልኩት የተሰራው ስራ እንደወርክሾፕ ይሆናል ብዬ በማመን ነው ::
ቸር ቆዩልኝ
_________________ ጥበብ ከእኔ የበለጠ ጠንካራ ናት እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን እሷ እንደፈለገችው ታደርገኛለች::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
-...- Joined: 09 Feb 2012 Posts: 312
Posted: Sun Apr 08, 2012 11:50 pm Post subject:
ዋናው እንደጻፈ(ች)ው : ምን ጎርጓሪ ምን ያወጣል ነው 'ሚባለው ...
አያረጉትም አይባልም ድሮም የወደቀ ዛፍ መጥረቢያ እንደሚበዛበት ይታወቃል ... ደግነቱ እሩብ ሚልዮን ዕይታን ያፈራች ጥላ ዓልባ አባቷ ማን እንደሆነ አይታወቅም ቢባል አይታመንም እናም ደፍረው ቢያደርጉት 'ንኳን ዋርካዊያን /ያት ተደራሲዎቼ ከመፀሐፉ ግርጌ ያለዉን የሀሰት ስም ፍቀው የባለቤቱን ስም እንደሚፅፉበት ጥርጣሬው የለኝም :: (ድሮም ዓላማዬ ቸብችቦ ሳንቲም ከመቁጠር ምናቤን በማጋራት ከምወደው ወገኔ ጋር በሀሳብ መገናኘት ነውና )
ስለጥላ -ዓልባ ከተነሳ መቼም ከዚህ በፊት የተኛ ቤት እንደሆነ እንጃ 'ንጂ አውርቼው ነበር የመቋረጡ ምክኒያት መካከለኛው ምስራቅ የሚታተም አንድ አበሻዊ መፀሔት ላይ በተከታታይ ክፍሎች እየወጣ መሆኑን ሳታውቁት አትቀሩም :: መጀመሪያ ላይ ብዙም ተቃውሞ አልነበረኝም ዋርካን ገልጠው ማንበብ ለማይችሉ መዳረሱንም ወድጄው ነበር ኋላ ግን የዋርካ ወንድምና እሕቶቼንም ምክር ስሰማ እኔም ከ 300 በላ ገፆች ያሉትን ስራ ለመፃፍ ካፈሰስኩት ጊዜ አኳያ ሳስበው ለዛዉም በቅጡ ፈቃድ ሳልጠየቅ ዝም ብዬ እነሆ በረከቱን ማለቱ ወደጅልነት ያመራብኝ መሰለኝ ::
በርግጥ የድርሰቱ መግቢያ ላይ እንዲህ የሚል ፅሑፍ አስፍሬ ነበር ታዲያ ኮፒራይቱ በሣይበር ኢቲዮጲያ አላፊነት ቢሆንም አደራ በመተማመን ይሁን አዎ ሳይበር ኢትዮጵያዎች እንደምናውቀው ዋርካችን በትክክል ለመስራቱ ሳይታክቱ ከመጣር ውጪ ለማንም ለምንም ግድ የላቸዉም ዋናው የሚባል አንድ ባተሌ ስለመኖሩ ሁሉ ላያውቁ ይችላሉ ያም ሆነ ይህ መተማመኑ ከጠፋ ጥላ -ዓልባ ለጊዜው ጥላ ስር አረፍ ብትልስ ብዬ ከጓሮ ሸጎጥኳት ብዙዎቹ እንደሚያደርጉት ላጲስ ይዤም አልተመለስኩባትም ::
ሞኝ የዘራውን ብልህ ያጭደዋል ይባላል :: ዋኒቾ ይበልህ :: 300 ገጽ ጽፈህ አመታት ሳታሳትመው 10 አመት ቁጭ ያልክበት ከመቃብር ድንጋይህ ላይ እንዲጻፍልህ ነው ? ከሰነፍክ እንደፓኑ ለዩኒቨርሲቲ ማተሚያ ቤት ስጠውና በስምህ ታትሞ ቅርስ ይሁንህ :: ሌባው ጠራዥማ ውስኪዉን ለብለብ አድርጎ ጣጥ ሲል ደራሲ ነኝ ግን የኛ ሕዝብ ጥሩ መጽሀፍ አፕሪሺየት አያደርግም ምክንያቱም 4700 ብቻ ነው የተሸጠልኝ እያለ ያማርራል :: አንጎሉና ህሊናው ያልተረዳው ነገር 4700 ኮፒ በ 20 ዶላር 94000 ዶላር ያልደከመበትና ለሱ የማይገባውን ማግኘቱ ነው :: _________________ እሰይ ተመስጌን አምላኬ ለካስ በክብርነቴ እራሴን ሆኜ እኔነቴን ፈልጌ አግኝቼዋለሁ !?
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator