View previous topic :: View next topic
Author
Message
ናፖሊዮን ዳኘ Joined: 18 Apr 2008 Posts: 1874
Posted: Mon Apr 16, 2012 3:48 am Post subject: ጥያቄ
http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
ከላይ ያስቀመጥኩት ርዕሱ ጎንደርኛ ይላል ... አሁን ይሄ ጎንደርኛ ነው ወይ ? አይደለም ጥያቄየ :: እንደዚህ አይነት የሙዚቃ ስራ ምን ያህል ገበያ አለው ኢትዮጵያ ውስጥ :: ሱሪ ዝቅ እያደረገ የሚለብስ ወጣት በገፍ እንዳለ የሰማሁት ዛሬ ነው :: በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ ፍሬንዶች እኔ ጋር ተሰብስበን ነበር :: ዮ ቲዮብ ዓለም ገብተን ስንዋኝ ይሄ ነገር አንዱ ጓደኛችን ማየት እንዳለብን ነገርን አየነው :: ከምር ግን እንደዚህ ሱሪ ዝቅ እያደረጉ የሚለብሱ ልጆች አሉ ማለት ነው ስል ....ብዙ ነገር ተቀያይሯል ከወጣህ ::
የምዕራብ ባህል በገፍ እየተስፋፋ ነው አለኝ :: ቀጠለ እና ቻይና እና ህንድ ባህልን በመጠበቅ በኩል የተሻሉ ናቸው :: ከሌላው ጋር አዳፕት ቢያደርጉም የራሳቸውን ግን በተዐምር አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነረ :: ቀጠለ ና ደሞ እኛ ሀገር ውስጥ ግን አሁን ባለው አያያዝ የሚቀጥለው "ጀነሬሽን " ሙሉ በሙሉ ራሱን እንሳይስት ያሰጋዋል አሉኝ :: በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውንም ሁኔታም ስለማላውቀው ቁጭት እና ዝምታ ዋጡኝ :: የምለውም ነገር ስለሌለኝ :: ስለ ጉዳዩ የምታውቁ እና የተሻለ ማብራራት የምትችሉ ማብራሪያ ብትሰጡኝ ? አዲሳባ ብቻ ነው በክፍለሀገርም እንዲህ ያለ ነገር ተዛምቷል ?? የችግሩስ ጥልቀት ምን ያህል ነው ??
ከምስጋና ጋር ::
ናፖሊዮን ዳኘ _________________ ሰው ህሊናውን የሚሸጠው ክህሊና በላይ ዋጋ ያለው ምን ነገር ሊገዛበት ነው?
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
የመረረው . Joined: 05 Mar 2012 Posts: 98 Location: USA
Posted: Mon Apr 16, 2012 2:50 pm Post subject:
ኢትዮጵያ ውስጥ የውጭ ባህል መስፋፋቱ አዲስ አይደለም :: ያኔ ገና ድሮ ከአገሬ ሳልወጣ ሰፈራችን ካለው ትልቅ ዋርካ ስር ቁጭ ብዬ አላፊ አግዳሚውን እያየው በትልቅ መፋቂያ ጥርሴን ስፍቅ ጎረቤታችን እትዬ አሰለፈች ""እንዴው ፈጣሪዬ ይሄ አማሪካ የሚባለውን አገር ሳታሳየኝ እንዳትገድለኝ "" ሲሉ ሰምቻቸው ሲገርመኝ እንደዋለ ትዝ ይለኛል ::
ዛሬ የምዕራቡ አለም ባህል ኢትዮጵያ ላይ አሻራውን አሳርፏል :: ለምሳሌ አዲስ ላይ ዞር ዞር ብትል የንግድ ቤቶቹን ስም መመልከት ቀላል ነው :: በሙሉ እንግሊዝኛ ነው :: ብራዘርስ ክሊኒክ የሚባል ሰፈራችን አቅራቢያ እንደነበረ ትዝ አይለኛል :: ይሄን ለምሳሌ ላንሳው እንጂ ብዙ ብዙ ስማቸውን የረሳውት ንግድ ቤቶች በአማርኛ ይፃፉት እንጂ ስማቸው እንግሊዝኛ ነው ::
ወጣቱን በተመለከተ ከአገር ከወጣህ ምን ይህል አመት እንደሆነህ ባላውቅም እኔ በነበርኩበት ግዜ እንኩዋን ሱሪያችንን ዝቅ እናደርግ ነበር :: ያኔ ታዲያ እነ 2pac የገነኑበት ዘመን ስለነበር አለባበሳችንም ከነሱ ጋር ለማመሳሰር ብዙ እንጥር ነበር :: በኃላ አባቴ ልብሴን አስተካክዬ ካለበስኩኝና ፅጉሬን በትክክል ካልተቆረጥኩኝ አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድብኝ ሲዝት ግዜ ተስተካከልኩኝ :: ግና ፋሽን መከተል አሁን የመጣ አይመስለኝም ለምሳሌ እነ አለማየው እሸቴንና የድሮ አራዳዎችን ብታያቸው ፀጉራቸውን ለምጥጠው ኮኛክ እየጠጡ ቡጊ ሲደንሱ ያመሹ ነበር :: ይሄ ታዲያ መቼም የኛ ካልቸር አይደለም :: እኔ ድሮ እነ ቱፓክን እንደዛ እንደምወዳቸው ዛሬ ወደ ፈረንጁ አለም መጥቼ ኑሮዬን ስጀምር ከምንም በላይ የራሴ ባህልና ሙዚቃ እየማረኩኝ መጡ ::
እና ታዲያ አሁን ያለው ወጣት ፋሽን ቢከተልም አብዛኛው ከፍ ሲልና ነብስ አውቆ ትዳር ሲጀምር ነገር አለሙን እርግፍ አድርጎ ይተወዋል :: ለሁሉም ግዜ አለው እንደሚባለው ኢትዮጵያ ፍንዳታዎቹ የነጩን አለም ባህል በልብስም በምንም ለመከተል ቢሞክሩም እድሜያቸው ገፍቶ ከፍ ሲሉ ድሮ እንደለመዱት እንሁን እንኳን ቢሉ የሰፈሩ ሰው ተረብ አያስቀምጣቸውም :: በስተርጅና ስትፈነዳ አይቶህ አንዱ የሰፈር ተረበኛ አንድ ነገር ጣል ቢያደርግብህ እንደ ጥቅምት ብርድ አጥንትህ ውስጥ ገብቶ ሲያንቀጠቅጥህ ነው የሚውለው :: ይልቅስ እዚ አሜሪካ ከመጣው ብዙ የሽማግሌ ፍንዳታ አይቻለው :: እድሜያቸው ከአገሩ ሲወጡ መቁጠር ያቆማል የተባሉ ይመስል እንደ ልጅ የሚያደርጋቸው ብዙ ሰዎችን አሉ :: በተረፈ አንድ ነገር ብዬ ልሰናበት , ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን ነበር ዥጉርጉርነቱን ሊለወጥ ይቻለዋል ? _________________ ----------Oooo---
-----------(----)---
------------)--/----
------------(_/-
----oooO----
----(---)----
-----\--(--
------\_)-
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ሓየት 11 Joined: 06 Apr 2008 Posts: 2735 Location: ላን'ሊይ
Posted: Tue Apr 17, 2012 11:05 am Post subject: Re: ጥያቄ
ይህን የሚጠይቀው ናፖሊዮን ነው እስኪ መጀመሪያ ስምህን ቀይረው ... ወሬኛ ... ... ገና ድሮ ካልጠፋ አገርኛ ስም የፈረንጅ ስም የመረጥክበት ምክንያት ራሱ ... ከነዚህ ልጆች የባሰ ነጭ አምላኪ ስለነበርክ አይደልም ዎይ ? ዛሬ ነው በባህልህና በማንነት መኩራት የታየህ
ሱሪ ዝቅ አድርገው መልበሳቸው ግርምት ፈጠረብህ አይደል ... ሱሪው ራሱ እኮ ያንተ ባህል አልነበርም ... ይሄኔ ያገለደምከውን ጨርቅ ገለብ አድርገህ ነበር ... እንደውሻ አጥር ተደግፈህ የምትሸናው
ሓየት
በዜጎች ነጻነት ጣልቃ የማይገባው
ናፖሊዮን ዳኘ እንደጻፈ(ች)ው : http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
ከላይ ያስቀመጥኩት ርዕሱ ጎንደርኛ ይላል ... አሁን ይሄ ጎንደርኛ ነው ወይ ? አይደለም ጥያቄየ :: እንደዚህ አይነት የሙዚቃ ስራ ምን ያህል ገበያ አለው ኢትዮጵያ ውስጥ :: ሱሪ ዝቅ እያደረገ የሚለብስ ወጣት በገፍ እንዳለ የሰማሁት ዛሬ ነው :: በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ ፍሬንዶች እኔ ጋር ተሰብስበን ነበር :: ዮ ቲዮብ ዓለም ገብተን ስንዋኝ ይሄ ነገር አንዱ ጓደኛችን ማየት እንዳለብን ነገርን አየነው :: ከምር ግን እንደዚህ ሱሪ ዝቅ እያደረጉ የሚለብሱ ልጆች አሉ ማለት ነው ስል ....ብዙ ነገር ተቀያይሯል ከወጣህ ::
የምዕራብ ባህል በገፍ እየተስፋፋ ነው አለኝ :: ቀጠለ እና ቻይና እና ህንድ ባህልን በመጠበቅ በኩል የተሻሉ ናቸው :: ከሌላው ጋር አዳፕት ቢያደርጉም የራሳቸውን ግን በተዐምር አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነረ :: ቀጠለ ና ደሞ እኛ ሀገር ውስጥ ግን አሁን ባለው አያያዝ የሚቀጥለው "ጀነሬሽን " ሙሉ በሙሉ ራሱን እንሳይስት ያሰጋዋል አሉኝ :: በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውንም ሁኔታም ስለማላውቀው ቁጭት እና ዝምታ ዋጡኝ :: የምለውም ነገር ስለሌለኝ :: ስለ ጉዳዩ የምታውቁ እና የተሻለ ማብራራት የምትችሉ ማብራሪያ ብትሰጡኝ ? አዲሳባ ብቻ ነው በክፍለሀገርም እንዲህ ያለ ነገር ተዛምቷል ?? የችግሩስ ጥልቀት ምን ያህል ነው ??
ከምስጋና ጋር ::
ናፖሊዮን ዳኘ
_________________ An eye for an eye, and the whole world would be blind. (KGK)
>>>>>>>>> ገዛ ሓየት
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እናመሰግንሃለ Joined: 01 Jun 2009 Posts: 805
Posted: Tue Apr 17, 2012 3:58 pm Post subject: Re: ጥያቄ
ሓየት 11 እንደጻፈ(ች)ው : ይህን የሚጠይቀው ናፖሊዮን ነው እስኪ መጀመሪያ ስምህን ቀይረው ... ወሬኛ ... ... ገና ድሮ ካልጠፋ አገርኛ ስም የፈረንጅ ስም የመረጥክበት ምክንያት ራሱ ... ከነዚህ ልጆች የባሰ ነጭ አምላኪ ስለነበርክ አይደልም ዎይ ? ዛሬ ነው በባህልህና በማንነት መኩራት የታየህ
ሱሪ ዝቅ አድርገው መልበሳቸው ግርምት ፈጠረብህ አይደል ... ሱሪው ራሱ እኮ ያንተ ባህል አልነበርም ... ይሄኔ ያገለደምከውን ጨርቅ ገለብ አድርገህ ነበር ... እንደውሻ አጥር ተደግፈህ የምትሸናው
ሓየት
በዜጎች ነጻነት ጣልቃ የማይገባው
ናፖሊዮን ዳኘ እንደጻፈ(ች)ው : http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
ከላይ ያስቀመጥኩት ርዕሱ ጎንደርኛ ይላል ... አሁን ይሄ ጎንደርኛ ነው ወይ ? አይደለም ጥያቄየ :: እንደዚህ አይነት የሙዚቃ ስራ ምን ያህል ገበያ አለው ኢትዮጵያ ውስጥ :: ሱሪ ዝቅ እያደረገ የሚለብስ ወጣት በገፍ እንዳለ የሰማሁት ዛሬ ነው :: በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ ፍሬንዶች እኔ ጋር ተሰብስበን ነበር :: ዮ ቲዮብ ዓለም ገብተን ስንዋኝ ይሄ ነገር አንዱ ጓደኛችን ማየት እንዳለብን ነገርን አየነው :: ከምር ግን እንደዚህ ሱሪ ዝቅ እያደረጉ የሚለብሱ ልጆች አሉ ማለት ነው ስል ....ብዙ ነገር ተቀያይሯል ከወጣህ ::
የምዕራብ ባህል በገፍ እየተስፋፋ ነው አለኝ :: ቀጠለ እና ቻይና እና ህንድ ባህልን በመጠበቅ በኩል የተሻሉ ናቸው :: ከሌላው ጋር አዳፕት ቢያደርጉም የራሳቸውን ግን በተዐምር አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነረ :: ቀጠለ ና ደሞ እኛ ሀገር ውስጥ ግን አሁን ባለው አያያዝ የሚቀጥለው "ጀነሬሽን " ሙሉ በሙሉ ራሱን እንሳይስት ያሰጋዋል አሉኝ :: በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውንም ሁኔታም ስለማላውቀው ቁጭት እና ዝምታ ዋጡኝ :: የምለውም ነገር ስለሌለኝ :: ስለ ጉዳዩ የምታውቁ እና የተሻለ ማብራራት የምትችሉ ማብራሪያ ብትሰጡኝ ? አዲሳባ ብቻ ነው በክፍለሀገርም እንዲህ ያለ ነገር ተዛምቷል ?? የችግሩስ ጥልቀት ምን ያህል ነው ??
ከምስጋና ጋር ::
ናፖሊዮን ዳኘ
ኃየት ይቅርታ አድርግልኝና አስተያየትህ ይደብራል ::
ናፖልዮን ሁለት ነገሮችን ጠቁሟል :-
1- ጓደኛዬ ሲያወራልኝ ሕንዶችና ቻይናዎች ከሌሎች ጋር አዳፕት ያደርጋሉ ግን የራሳቸውን አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነዘረ ብሏል :: እኛም በተወሰነ መልኩ አዳፕት ብናደርግ ችግር የለውም :: እንዳውም አስፈላጊም ነው :: ችግሩ የራሳችንን መርሳቱ ላይ ነው :: የናፖልዮንም ጥቆማ ይሄ መሰለኝ ::
2- ደግሞም ከልብሱ ይልቅ ከልብሱ በታች ያለው ሥነልቦናና በስፋት የጄኔሬሽኑን አካሄድ መበረዙ መሰለኝ ማተር የሚያደርገው :: ስለዚህ ጉዳዩን ናፖልዮን በጥያቄ ምልክት "የችግሩ ጥልቀት ምን ያህል ነው ?" ብሎ ጠይቆ ማቆሙ ለውይይት በር ይከፍታል እንጂ እንደጭፍን ተቃውሞ ተቆጥሮ የሚያስወግዝ መሆን የለበትም :: በግለሰብ ነጻነት ካመንክ የናፖልዮንንም ኮንሰርን የመግለጽ መብቱን ማንቋሸሽ እንደማይገባህ ማወቅ አለብህ :: ይሄ የማንኛውም አገር ኮንሰርን ነው :: ሌላው ቀርቶ የነአሜሪካም ኮንሰርን ነው :: ባሕሎችን በሙሉ ዌልካም ቢያደርጉም ማንም የባሕል ወረራ እንዲያካሂድባቸው ግን አይፈልጉም :: ሚሼል ባክማን እንዳለችው የኛ የነጮች ካልቸር ከሌላው ይበልጣል - ስለሚበልጥም ነው ፈልገውን የመጡት - እናም ለኛ ካልቸር እንጂ ለኢሚግራንት ካልቸር ቅድሚያ መስጠት የለብንም ብላ ታምናለች (እሱን እንኳን ተዪው ! ደግሞ የበዝባዥ ካልቸር ብንላትም በሆዳችን )::
ደግሞም ችግሩ ጥልቀት ስላለው መስሎኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአገሩ ሰርቶ ለመኖር ያለውን ኦፕሽን ኤግዞስት ሳያደርግ በየብስ በባሕር በአየር ከአገር መውጣትን ብቻ እያለመ በምኞት መንምኖ የሚኖረው ! እና በግለሰብ ነጻነት ማመን ማለት ትውልድ ራሱን እያጣ ሲመጣ "ኖ ኮሜንት " ብሎ አይድል መሆን ማለት አይደለም :: መላ መምታት ግድ ነው :: ያ ደግሞ ከውይይት ይጀምራል ::
እና አስተያየትህ ይደብራል :: ፐርሰናል ፐርሰናል ይሸታል ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ናፖሊዮን ዳኘ Joined: 18 Apr 2008 Posts: 1874
Posted: Tue Apr 17, 2012 7:22 pm Post subject:
የመረረህ
ምን መሰለህ የባልህ ልውውጥ እኮ አለ :: ይኖራልም :: ባለፉት ሀያ አመታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እንደመሰደዳቸው እና በተሰደዱበትም የምዕራብ ዓለም "ፊት ' ማድረግ ስላለባቸው ተመሳስለው ባህሉ ተዋህዶቸው ያንን ወደ ኢትዮጵያ በተለያየ መልክ እያስገቡ ታናናሾቻቸው ላይ እንደሚያዛምቱት ግልጸ ነው ::
ከዚያም በፊት እኔ ኢትዮጵያ እያለሁ በስድስት ኪሎ ዋናው ጊቢ ሱሪያቸውን ዝቅ እያደረጉ የሚለብሱ አንዳንድ አይጠፉም ነበር :: ሜይን ስትሪም ስታይል ግን አልነበረም :: የኔ ኮንሰርን የተጽዕኖው መጠን የጠነከረ መሰለኝ ነው :: እንዴት ብንመቻቸው ነው ???
እንግዲህ ጎንደር በባህላዊነቱ የሚታወቅ አርበኝነትም ጭምር ያለበት ሀገር ነው :: የጎንደር ምቱ ሌላ ነው "" መገርን አርማጭሆ ወልቃይት ጠገዴ ነው "" (እውነት አርማጭሆ እና ጠገዴ ለህወሀት ሲገዛ ሚገርም ነው ) አትንኩኝ ባይነት ያለበት ያገር ፍቅር ያለበት ----እንደ ኮርም የሚታይ ነው ::
ሊያፈራርሷት ያሰቧትን ባህል ምን ይሏታል እንደሚባለው ቲፒካል ባህላዊ እሴት ያለበትን የጎንደር ባህል ---በራፕኛ እየነካኩ ነገ ባለ የጎንደር ባለማሲንቆ ራፕር ካልሆንኩ እንደማይል ምንም ማረጋገጫ የለውም ::
ጥያቄው ይጠቅመናል ወይ ነው ?? በጣም ዋጋ የምንሰጠውን ነገር ለማዳን ይጠቅመናል ወይ ነው ?? በዛ ላይ ብልጥ ሰው የነዚህ የራፕር ግሩፖችን እና ሶንጉን የጻፉትን ስዎች አዋዋል እና ኮኔክሽን በማያስታውቅ መንገድ ቢያጠና ...ምናልባት ከኍላቸው ባህል ሬፕ ሊያደርግ እየሞከራ ያለ አጋፋሪ እይጠፋም :: አካሄዳቸው እንደዚሁ ስለሆነ ነው :: ባለቤት የሌለው ባህል ሆነ እኮ የኛ ነገር ::
የተሰማኝን በውል እንደገለጽኩት ርግጠኛ አይደለሁም :: የጎንደር ውበቱ ጎንደርኛ ነው :: የኢትዮጵያም ሀብት ነው :: ከላይ ባስቀመጥኩት ክሊፕ ላይ ጎንደርኛ እያሉ ያላገጡትን ከስድብ እና በሰው አይደንቲቲ ከመጫወት ለይቼ አላየውም :: አላማም ያለው ይመስለኛል ::
ናፖሊዮን ዳኘ ::
የመረረው . እንደጻፈ(ች)ው : ኢትዮጵያ ውስጥ የውጭ ባህል መስፋፋቱ አዲስ አይደለም :: ያኔ ገና ድሮ ከአገሬ ሳልወጣ ሰፈራችን ካለው ትልቅ ዋርካ ስር ቁጭ ብዬ አላፊ አግዳሚውን እያየው በትልቅ መፋቂያ ጥርሴን ስፍቅ ጎረቤታችን እትዬ አሰለፈች ""እንዴው ፈጣሪዬ ይሄ አማሪካ የሚባለውን አገር ሳታሳየኝ እንዳትገድለኝ "" ሲሉ ሰምቻቸው ሲገርመኝ እንደዋለ ትዝ ይለኛል ::
ዛሬ የምዕራቡ አለም ባህል ኢትዮጵያ ላይ አሻራውን አሳርፏል :: ለምሳሌ አዲስ ላይ ዞር ዞር ብትል የንግድ ቤቶቹን ስም መመልከት ቀላል ነው :: በሙሉ እንግሊዝኛ ነው :: ብራዘርስ ክሊኒክ የሚባል ሰፈራችን አቅራቢያ እንደነበረ ትዝ አይለኛል :: ይሄን ለምሳሌ ላንሳው እንጂ ብዙ ብዙ ስማቸውን የረሳውት ንግድ ቤቶች በአማርኛ ይፃፉት እንጂ ስማቸው እንግሊዝኛ ነው ::
ወጣቱን በተመለከተ ከአገር ከወጣህ ምን ይህል አመት እንደሆነህ ባላውቅም እኔ በነበርኩበት ግዜ እንኩዋን ሱሪያችንን ዝቅ እናደርግ ነበር :: ያኔ ታዲያ እነ 2pac የገነኑበት ዘመን ስለነበር አለባበሳችንም ከነሱ ጋር ለማመሳሰር ብዙ እንጥር ነበር :: በኃላ አባቴ ልብሴን አስተካክዬ ካለበስኩኝና ፅጉሬን በትክክል ካልተቆረጥኩኝ አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድብኝ ሲዝት ግዜ ተስተካከልኩኝ :: ግና ፋሽን መከተል አሁን የመጣ አይመስለኝም ለምሳሌ እነ አለማየው እሸቴንና የድሮ አራዳዎችን ብታያቸው ፀጉራቸውን ለምጥጠው ኮኛክ እየጠጡ ቡጊ ሲደንሱ ያመሹ ነበር :: ይሄ ታዲያ መቼም የኛ ካልቸር አይደለም :: እኔ ድሮ እነ ቱፓክን እንደዛ እንደምወዳቸው ዛሬ ወደ ፈረንጁ አለም መጥቼ ኑሮዬን ስጀምር ከምንም በላይ የራሴ ባህልና ሙዚቃ እየማረኩኝ መጡ ::
እና ታዲያ አሁን ያለው ወጣት ፋሽን ቢከተልም አብዛኛው ከፍ ሲልና ነብስ አውቆ ትዳር ሲጀምር ነገር አለሙን እርግፍ አድርጎ ይተወዋል :: ለሁሉም ግዜ አለው እንደሚባለው ኢትዮጵያ ፍንዳታዎቹ የነጩን አለም ባህል በልብስም በምንም ለመከተል ቢሞክሩም እድሜያቸው ገፍቶ ከፍ ሲሉ ድሮ እንደለመዱት እንሁን እንኳን ቢሉ የሰፈሩ ሰው ተረብ አያስቀምጣቸውም :: በስተርጅና ስትፈነዳ አይቶህ አንዱ የሰፈር ተረበኛ አንድ ነገር ጣል ቢያደርግብህ እንደ ጥቅምት ብርድ አጥንትህ ውስጥ ገብቶ ሲያንቀጠቅጥህ ነው የሚውለው :: ይልቅስ እዚ አሜሪካ ከመጣው ብዙ የሽማግሌ ፍንዳታ አይቻለው :: እድሜያቸው ከአገሩ ሲወጡ መቁጠር ያቆማል የተባሉ ይመስል እንደ ልጅ የሚያደርጋቸው ብዙ ሰዎችን አሉ :: በተረፈ አንድ ነገር ብዬ ልሰናበት , ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን ነበር ዥጉርጉርነቱን ሊለወጥ ይቻለዋል ?
_________________ ሰው ህሊናውን የሚሸጠው ክህሊና በላይ ዋጋ ያለው ምን ነገር ሊገዛበት ነው?
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ሓየት 11 Joined: 06 Apr 2008 Posts: 2735 Location: ላን'ሊይ
Posted: Tue Apr 17, 2012 7:47 pm Post subject: Re: ጥያቄ
ጤና ይስጥልኝ ወንድሜ
ሰሞኑን ስከታተልህ ጊደሮቹን ለመምሰል ራስህን እየተፈታተንከው እንዳለህ ነው ::
በርግጥ የጻፍኩት አልተመቸህ ሊሆን ይችላል :: ጉዳዩ ግን ፐርሰናል ሳይሆን ኦብጀክቲቭ ነው :: እውነትና የማምንበት ነው ::
የባህል ወረራን የምደግፍ ሰው ሆኜ አይደለም ይህን የምለው :: የሚጠቅምና የማይጠቅመውን መለየት የሚጎዳውንና የማይጎዳውን መለየት የተጠቃሚው ብቻ ሳይሆን የተቺውም ሀላፊነት ነው መሆን ያለበት :: ዘፈን ስለተወራረሰ ወይም አለባበስ ስለተወራረሰ እንደ ትልቅ ኢሹ የሚያይ ሰው ጽንፈኛ ሰው ብቻ ነው :: ናፖሊዮን ዛሬ ብቻ አይደለም ሁሌም ከፌስቡክ ይዟቸው የሚመጣ ጥቃቅን ኢሹዎች አሉ እንደ ትልቅ ኢሹ እዚህ እያመጣ የሚያነሳው :: እንደነዚህ አይነት ሰዎች ሀላፊነቱ ቢኖራቸው ዜጋውን የሚያፈናፍኑት አይሆኑም :: የሚገርመው ደግሞ ሊወቅሳቸው ከሚሞክር ታዳጊዎች በላይ ራሱ የባዕድ አምልኮ ተጠቂ መሆኑ ነው :: እስኪ ይህን ስሙን የመረጠበት ምክንያት ያጫውተን
የውልህ ወንድሜ ... አንተ አስተዋይ የእምነት ሰው ነበርክ ... የነዚህ ሰዎች አስተያየት ግን ይዞህ እየነጎደ ያለ ይመስለኛል
ቻቺ ታደሰ በዘመኗ ከውጪ ዘፈን ውጪ ኢትዮጵያዊ ዘፈኖችን ብዙ ያልሞካከረች ነበረች :: ማንም ኢትዮጵያዊ ማንነቷን እንደለወጠች ሲወቅሳት ሰምቼ አላውቅም :: ሙዚቃ እኮ ድንበር አይወስነውም :: ኢትዮጵያዊውም የውጪ ዘፈን ያምረዋል :: እንደ ቻቺ አይነት አገርና ወገን ወዳድ ሰዎች ከማህበረሰባቸው ብዙ ሳይርቁ የሌላውን ባህል ወርሰው ኖረዋል :: ከኢትዮጵያ አርቲስቶች በህዝብ የተወደሰ ማን እንደቻቺ ይኖራል ?
እነዚህ ታዳጊዎችም በነሱ ዕድሜ የሚገኙ ወገኖቻቸው በሚወዱት መልኩ ዘፍናቸውንና ዳንሳቸውን ቢቀያይጡት ምንም ጎጂ የሚባል ነገር አይታየኝም እኔ :: ዘፈኑ አገርኛ ጭፈራው አገርኛውን ለዛ ሳይለቅ ... አለባበሳቸውና አክታቸውም ከዘፈኑ ስልት ጋር የሚሄድ ... ምንድን ነው ችግሩ ? ... ሽሩባ ቢሰሩና ሎቲ ቢያጠልቁስ ምን እንል ነበር ... ሙልጭ አድርገን እንወቅሳቸው ነበር ? ሎቲውና ሹርባው በኢትዮጵያ ምድር በቅሎ እንዳልተሰደደ
ማውገዝ ሌላ ነው :: የሚወገዝ ... ከውጪ የተወረሰ የፖለቲካ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ :: ከውጪ የተወረሰ የንግድ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ :: ከውጪ የተወረሰ የመማርና የማስተማር ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ :: ከውጪ የተወረሰ ... የቤተሰብ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ :: ... ወዘተ
እነዚህ ናቸው ህልውናችንን የሚፈታተኑት እንጂ አንድ ሁለት ታዳጊ ወጣቶች የውጭ ዳንኪራ ስለደቁ ወይም ከአገርኛው ጋር ስለቀየጡት ወይም ሱሪያቸውን ዝቅ አድርገው ስለለበሱ ... የአገር ህልውና የሚፈታተን አይደለም :: እዚህ በሰለጠነው አለምም እኮ (የመረረው እንዳለው ) በታዳጊነታቸው ሀፈርተ ስጋቸውን ሁሉ ከፋፍተው የሚሄዱ ሰዎች ከዕድሜ ጋር ሲሰክኑ ወደ ማንነታቸው ይመለሳል :: ይልቅስ ስር ከያዘ የማይነቀለውን ሌላ የባዕድ ባህል ነው ማውገዝ ::
ይሄ በረባ ባልረባ ታዳጊዎችን መኮነን ለእኔ ትምክህተኝነት ነው :: ... እኔ የማዳምጠው ዘለሰኛ : የምወርደው እስክስታ ወይም የምለብሰው የክት ልብስ ብቻ ነው ትክክል ማለት ተመጻዳቂ መሆን ብቻ ነው ትርፉ :: አይመስልህ ?
ሓየት
እናመሰግንሃለ� እንደጻፈ(ች)ው : ሓየት 11 እንደጻፈ(ች)ው : ይህን የሚጠይቀው ናፖሊዮን ነው እስኪ መጀመሪያ ስምህን ቀይረው ... ወሬኛ ... ... ገና ድሮ ካልጠፋ አገርኛ ስም የፈረንጅ ስም የመረጥክበት ምክንያት ራሱ ... ከነዚህ ልጆች የባሰ ነጭ አምላኪ ስለነበርክ አይደልም ዎይ ? ዛሬ ነው በባህልህና በማንነት መኩራት የታየህ
ሱሪ ዝቅ አድርገው መልበሳቸው ግርምት ፈጠረብህ አይደል ... ሱሪው ራሱ እኮ ያንተ ባህል አልነበርም ... ይሄኔ ያገለደምከውን ጨርቅ ገለብ አድርገህ ነበር ... እንደውሻ አጥር ተደግፈህ የምትሸናው
ሓየት
በዜጎች ነጻነት ጣልቃ የማይገባው
ናፖሊዮን ዳኘ እንደጻፈ(ች)ው : http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
http://youtu.be/pJEeibMm_Zc
ከላይ ያስቀመጥኩት ርዕሱ ጎንደርኛ ይላል ... አሁን ይሄ ጎንደርኛ ነው ወይ ? አይደለም ጥያቄየ :: እንደዚህ አይነት የሙዚቃ ስራ ምን ያህል ገበያ አለው ኢትዮጵያ ውስጥ :: ሱሪ ዝቅ እያደረገ የሚለብስ ወጣት በገፍ እንዳለ የሰማሁት ዛሬ ነው :: በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ ፍሬንዶች እኔ ጋር ተሰብስበን ነበር :: ዮ ቲዮብ ዓለም ገብተን ስንዋኝ ይሄ ነገር አንዱ ጓደኛችን ማየት እንዳለብን ነገርን አየነው :: ከምር ግን እንደዚህ ሱሪ ዝቅ እያደረጉ የሚለብሱ ልጆች አሉ ማለት ነው ስል ....ብዙ ነገር ተቀያይሯል ከወጣህ ::
የምዕራብ ባህል በገፍ እየተስፋፋ ነው አለኝ :: ቀጠለ እና ቻይና እና ህንድ ባህልን በመጠበቅ በኩል የተሻሉ ናቸው :: ከሌላው ጋር አዳፕት ቢያደርጉም የራሳቸውን ግን በተዐምር አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነረ :: ቀጠለ ና ደሞ እኛ ሀገር ውስጥ ግን አሁን ባለው አያያዝ የሚቀጥለው "ጀነሬሽን " ሙሉ በሙሉ ራሱን እንሳይስት ያሰጋዋል አሉኝ :: በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውንም ሁኔታም ስለማላውቀው ቁጭት እና ዝምታ ዋጡኝ :: የምለውም ነገር ስለሌለኝ :: ስለ ጉዳዩ የምታውቁ እና የተሻለ ማብራራት የምትችሉ ማብራሪያ ብትሰጡኝ ? አዲሳባ ብቻ ነው በክፍለሀገርም እንዲህ ያለ ነገር ተዛምቷል ?? የችግሩስ ጥልቀት ምን ያህል ነው ??
ከምስጋና ጋር ::
ናፖሊዮን ዳኘ
ኃየት ይቅርታ አድርግልኝና አስተያየትህ ይደብራል ::
ናፖልዮን ሁለት ነገሮችን ጠቁሟል :-
1- ጓደኛዬ ሲያወራልኝ ሕንዶችና ቻይናዎች ከሌሎች ጋር አዳፕት ያደርጋሉ ግን የራሳቸውን አይለቁም የሚል ሀሳብ ተሰነዘረ ብሏል :: እኛም በተወሰነ መልኩ አዳፕት ብናደርግ ችግር የለውም :: እንዳውም አስፈላጊም ነው :: ችግሩ የራሳችንን መርሳቱ ላይ ነው :: የናፖልዮንም ጥቆማ ይሄ መሰለኝ ::
2- ደግሞም ከልብሱ ይልቅ ከልብሱ በታች ያለው ሥነልቦናና በስፋት የጄኔሬሽኑን አካሄድ መበረዙ መሰለኝ ማተር የሚያደርገው :: ስለዚህ ጉዳዩን ናፖልዮን በጥያቄ ምልክት "የችግሩ ጥልቀት ምን ያህል ነው ?" ብሎ ጠይቆ ማቆሙ ለውይይት በር ይከፍታል እንጂ እንደጭፍን ተቃውሞ ተቆጥሮ የሚያስወግዝ መሆን የለበትም :: በግለሰብ ነጻነት ካመንክ የናፖልዮንንም ኮንሰርን የመግለጽ መብቱን ማንቋሸሽ እንደማይገባህ ማወቅ አለብህ :: ይሄ የማንኛውም አገር ኮንሰርን ነው :: ሌላው ቀርቶ የነአሜሪካም ኮንሰርን ነው :: ባሕሎችን በሙሉ ዌልካም ቢያደርጉም ማንም የባሕል ወረራ እንዲያካሂድባቸው ግን አይፈልጉም :: ሚሼል ባክማን እንዳለችው የኛ የነጮች ካልቸር ከሌላው ይበልጣል - ስለሚበልጥም ነው ፈልገውን የመጡት - እናም ለኛ ካልቸር እንጂ ለኢሚግራንት ካልቸር ቅድሚያ መስጠት የለብንም ብላ ታምናለች (እሱን እንኳን ተዪው ! ደግሞ የበዝባዥ ካልቸር ብንላትም በሆዳችን )::
ደግሞም ችግሩ ጥልቀት ስላለው መስሎኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአገሩ ሰርቶ ለመኖር ያለውን ኦፕሽን ኤግዞስት ሳያደርግ በየብስ በባሕር በአየር ከአገር መውጣትን ብቻ እያለመ በምኞት መንምኖ የሚኖረው ! እና በግለሰብ ነጻነት ማመን ማለት ትውልድ ራሱን እያጣ ሲመጣ "ኖ ኮሜንት " ብሎ አይድል መሆን ማለት አይደለም :: መላ መምታት ግድ ነው :: ያ ደግሞ ከውይይት ይጀምራል ::
እና አስተያየትህ ይደብራል :: ፐርሰናል ፐርሰናል ይሸታል ::
_________________ An eye for an eye, and the whole world would be blind. (KGK)
>>>>>>>>> ገዛ ሓየት
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እናመሰግንሃለ Joined: 01 Jun 2009 Posts: 805
Posted: Wed Apr 18, 2012 1:04 am Post subject: Re: ጥያቄ
ሓየት 11 እንደጻፈ(ች)ው : ጤና ይስጥልኝ ወንድሜ
ሰሞኑን ስከታተልህ ጊደሮቹን ለመምሰል ራስህን እየተፈታተንከው እንዳለህ ነው ::
ማናቸው ደግሞ "ጊደሮች "?
"ራስን መፈታተን "ስ ምንድነው ?
Quote: የባህል ወረራን የምደግፍ ሰው ሆኜ አይደለም ይህን የምለው :: የሚጠቅምና የማይጠቅመውን መለየት የሚጎዳውንና የማይጎዳውን መለየት የተጠቃሚው ብቻ ሳይሆን የተቺውም ሀላፊነት ነው መሆን ያለበት ::
ስለዚህ ባጭሩ ናፖልዮን 'ኮ ይህንን ነው የሚልህ ያለው ? አይደለም እንዴ ?
በሌላ ቋንቋ ሳስቀምጥልህ : ባንተ አስተያየት ቪድዮው ላይ የሚታዩት ልጆች የባሕል ወረራ ተጠቂዎች ናቸው ብለን መደምደም እንችላለን ? ካልሆነ እንዴት ? አንተ በግልህ የባሕል ወረራን የምትቃወም ከሆነ : ይሄ የምናየው ቪድዮ የባሕል ወረራ ነጸብራቅ ነው ወይስ አይደለም ነው ጥያቄው :: በዚያ ዙርያ አስተያየት ብትሰጥ የዐምዱን ግብ መታህ ማለት ነው ::
ከሆኑ ደግሞ ምን ይሻላል ? ይህ የጥቂቶች ምርጫ ነው ወይስ የትውልዱ ትሬንድ በዚህ መልኩ እየሄደ ነው ? ባጭሩ የችግሩ ስፋትና ጥልቀት ምን ያህል ነው ?
Quote: ባጭሩ - ዘፈን ስለተወራረሰ ወይም አለባበስ ስለተወራረሰ እንደ ትልቅ ኢሹ የሚያይ ሰው ጽንፈኛ ሰው ብቻ ነው ::
ዘፈንም አለባበስም ይወራረሳል :: ቢሆንም አዳፕት ተደርጎ አገርኛ መልክ ካልተሰጠው በፍጹም የራስ ሊሆን አይችልም :: የራስን ጥሎ ሌላውን ማንጠልጠል ግን አይደንቲቲ ክራይሲስ ያደርሳል :: ይሄ የጽንፈኞች አስተሳሰብ ሳይሆን ግልጽ እውነታ ነው :: በተለይ አፍሪካውያን የተጠቁበት ::
በነገርህ ላይ በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን አይዶሏ ዳኛ የሺ : በኢትዮጵያ ሙዚቃ አካሄድና አዝማሚያ ዙርያ ሥጋት እንዳላትና እንደሚያሳዝናት ተናግራ ነበር ::ምን ይደረግ ! ባለሙያ ልጥቀስልህ እንጂ ለግልጹ ጉዳይ !!
Quote: ናፖሊዮን ዛሬ ብቻ አይደለም ሁሌም ከፌስቡክ ይዟቸው የሚመጣ ጥቃቅን ኢሹዎች አሉ እንደ ትልቅ ኢሹ እዚህ እያመጣ የሚያነሳው ::
ለዛ 'ኮ ነው ፐርሰናል ፐርሰናል ይሸታል የምልህ - አስተያየትህ :: ከዚህ በፊት ስለተናደድክበት : አሁን በግልጹ ጉዳይ ላይም አስተያየትህ ጠንጋራ ነው - በናፖልዮን ስለተጻፈ ብቻ !
Quote: እንደነዚህ አይነት ሰዎች ሀላፊነቱ ቢኖራቸው ዜጋውን የሚያፈናፍኑት አይሆኑም ::
ዜጋቸውን ከባሕል ከወጋቸው እንዳይፈናፈኑ በሳማ እየለበለቡና እየቆነጠጡ ያሳድጉ የነበሩ ወላጆች : የኔታዎችና የሰፈር ሽማግሎች በነበሩበት ዘመን ኢትዮጵያ ሰውና እግዚአብሔር ተስማምታ የኖረችባት አገር ነበረች ::
ባንተ ግምት አሁን ትውልዱን በአለባበስ ልቅ የለቀቀው : በአስተሳሰብ ግን የማሰብና የመጠየቅ መብቱን ለምሑሩ ሳይቀር የነፈገው ይህ የዘመናችን መንግሥት ዜጋውን እያፈናፈነው ነው ማለትህ ነው ?
Quote: የሚገርመው ደግሞ ሊወቅሳቸው ከሚሞክር ታዳጊዎች በላይ ራሱ የባዕድ አምልኮ ተጠቂ መሆኑ ነው :: እስኪ ይህን ስሙን የመረጠበት ምክንያት ያጫውተን
ሊወቅሳቸው የሞከራቸው ታዳጊዎች የባዕድ አምላኪዎች መሆናቸውን ታምናለህ ማለት ነው ?
ኒኩን ናፖልዮን በማለቱ ደግሞ ናፖልዮን ከነርሱ በላይ የባዕዳን አምልኮ ያለበት ነው ብለህ ታምናለህ ማለት ነው ?
ኒክን ናፖልዮን ማለት እንዲህ ካስባለህ : ሱሪ ዝቅ አድርጎ በራፕ መጨፈር በርግጥም እልም ያለ የባእዳን አምልኮና የባሕል ወረራ ነው ማለት አይሆንም ?!
በርሱ ኒክ እንዲህ ከወሰንክ : ባንተው ዴፊኒሽን መሠረት : አንተው ራስህ "አክራሪ የማታፈናፍን " ነህ ማለት አይሆንም ?!
Quote:
የውልህ ወንድሜ ... አንተ አስተዋይ የእምነት ሰው ነበርክ ... የነዚህ ሰዎች አስተያየት ግን ይዞህ እየነጎደ ያለ ይመስለኛል
ማናቸው "እነዚህ " ሰዎች ? አንዱ ናፖልዮን መሆኑ ነው ? ሌሎቹስ ?
Quote: ቻቺ ታደሰ በዘመኗ ከውጪ ዘፈን ውጪ ኢትዮጵያዊ ዘፈኖችን ብዙ ያልሞካከረች ነበረች :: ማንም ኢትዮጵያዊ ማንነቷን እንደለወጠች ሲወቅሳት ሰምቼ አላውቅም ::
ትውልዱ በሙሉ አይደንቲቲ ክራይሲስ ውስጥ ገብቶ ይሆናላ ?! ወይም ደግሞ ቻቺ የውጭውን ከአገርኛው ጋር የምታቀላቅለውን ነገር እንደአዳፕቴሽን ቆጥሮላት ይሆናላ ?! ወይም "የዘንድሮ ልጆች ለየላቸው " ብሎ ትቷት ይሆናላ ?! ወይም እንደናፖልዮን ጥያቄ ሲያነሱ እንደመለስ ለርሷ ጥብቅና የሚቆሙ ሓየቶች በዝተው ይሆናላ ?!
Quote: ሙዚቃ እኮ ድንበር አይወስነውም :: ኢትዮጵያዊውም የውጪ ዘፈን ያምረዋል :: እንደ ቻቺ አይነት አገርና ወገን ወዳድ ሰዎች ከማህበረሰባቸው ብዙ ሳይርቁ የሌላውን ባህል ወርሰው ኖረዋል :: ከኢትዮጵያ አርቲስቶች በህዝብ የተወደሰ ማን እንደቻቺ ይኖራል ?
ኡ ኡ ኡ ኡ ...! በጣም ያጋነንከው አይመስልህም ? ነው ወይስ መለስ አወደሰ ማለት ሕዝብ አወደሰ ማለት ነው ?
እኔ እቅጩን ልንገርህና ልጅ ሆኜ ቻቺ በጣም ክሬቲቭ ለመሆን ሌት ተቀን የምትሞክር ሆና እያለ ሕዝቡ ግን ብዙም የማያስታውሳት እንደሆነ ነው ይሰማኝ የነበረው - እንኳንስ ሕዝብ አወድሷታል ብዬ ላምን ቀርቶ :: ከአንድ የሙዚቃ ሰው ጋር ስነጋገር ግን "ቻቺ ያለጊዜዋ የተፈጠረች ናትና ብዙም ዕድል አልቀናትም :: ማኅበረሰቡ ይህን ያህልም የምዕራባውያኑን ሙዚቃ ሳይለምድ ስለተነሳች ሕዝብ ልብ ውስጥ የፈለገችውን ያህል አልገባችም " አለኝ :: ልክ ነው ብዬ ተስማማሁ :: የሚገርመው አሁን የምዕራባውያን ዘፈን በጣም ከተለመደም እንኳ በኋላ ቻቺ ሕዝብ ልብ ውስጥ አልገባችም :: ለማስረጃ የኢትዮጵያ ሙዚቃዎች ድኅረ ገጾችን ብትመለከት : ብዙ ዘፋኞች ስማቸውና አልበም ትራክ ሊስታቸው ሲኖር (እነ ሐመልማልና ኅብስትን ጨምሮ ): ቻቺ ግን የለችም ::
እንዲህ ቻቺን ከሌላው በተለየ ሁኔታ በሕዝብ የተወደሰች ብለህ ልታሞካሻት መሞከርህ : 1 መለስንና 80,000,000 ሕዝብን እኩል አድርገህ የምትመለከት እልም ያልክ የመለስ ባርያ መኃይም ወያኔ መሆንህን ያሳያል ::
Quote: እነዚህ ታዳጊዎችም በነሱ ዕድሜ የሚገኙ ወገኖቻቸው በሚወዱት መልኩ ዘፍናቸውንና ዳንሳቸውን ቢቀያይጡት ምንም ጎጂ የሚባል ነገር አይታየኝም እኔ :: ዘፈኑ አገርኛ ጭፈራው አገርኛውን ለዛ ሳይለቅ ... አለባበሳቸውና አክታቸውም ከዘፈኑ ስልት ጋር የሚሄድ ... ምንድን ነው ችግሩ ? ... ሽሩባ ቢሰሩና ሎቲ ቢያጠልቁስ ምን እንል ነበር ... ሙልጭ አድርገን እንወቅሳቸው ነበር ? ሎቲውና ሹርባው በኢትዮጵያ ምድር በቅሎ እንዳልተሰደደ
ናፖልዮንን ፐርሰናሊ ከመውቀስና ጭራሽ እንዲህ ያለ ጥያቄ መነሳቱን ከመቃወምህ በፊት : ይህን አሳብ በቅድሚያ ሰጥተህ ቢሆን ኖሮ : ትንሽም ቢሆን ለዛ ያለው ክርክር ተከራከርክ ይባል ነበር :: ባንተ ሃሳብ መስማማት አለመስማማት ያንባቢ ፈንታ ነው ::
ከማውገዝ በፊት ስለችግሩ ስፋትና ጥልቀት መወያየት አለብን :: ናፖልዮን ውግዘት ጋር የደረሰ አይመስለኝም ::
Quote: የሚወገዝ ... ከውጪ የተወረሰ የፖለቲካ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ ::
ምን አይነት የፖለቲካ ባሕል ነው እሱ ?
Quote: ከውጪ የተወረሰ የንግድ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ ::
እሱ ደግሞ ምን አይነት ነው ?
Quote: ከውጪ የተወረሰ የመማርና የማስተማር ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ ::
እሱስ የትኛው ነው ? ለይተህ ብታስረዳኝ ጥሩ ነው :: አፒታይቴን ከፍተኸዋል .....
Quote: ከውጪ የተወረሰ ... የቤተሰብ ባህል አለ ... እሱን ነው ማውገዝ :: ... ወዘተ
ስፔሲፊካሊ የትኛው ? እረ አስረዳኝ ?!
Quote: እነዚህ ናቸው ህልውናችንን የሚፈታተኑት እንጂ አንድ ሁለት ታዳጊ ወጣቶች የውጭ ዳንኪራ ስለደቁ ወይም ከአገርኛው ጋር ስለቀየጡት ወይም ሱሪያቸውን ዝቅ አድርገው ስለለበሱ ...
ኦኬ .... እንግዲህ የችግሩ ስፋት ወይም ጥልቀት ከአንድ ወይም ከሁለት ልጆች ያልዘለለ ከሆነ ጥሩ :: ችግሩ በዚሁ የተገደበ መሆኑን በማስረጃ ወይም በሰማኸው መጠን ምንጭ ጠቅሰህም ቢሆን ብታስረዳን የቤቱን ዓላማ አራመድክ ማለት ነው :: ጉዳዩ ለውይይት መክፈቻ ከናፖልዮን የተሰነዘረ ጥያቄ ስለሆነ ::
Quote: እዚህ በሰለጠነው አለምም እኮ (የመረረው እንዳለው ) በታዳጊነታቸው ሀፈርተ ስጋቸውን ሁሉ ከፋፍተው የሚሄዱ ሰዎች ከዕድሜ ጋር ሲሰክኑ ወደ ማንነታቸው ይመለሳል ::
የሰለጠነውን ዓለም የሰለጠነ ያደረጉት እነዚህ ሐፍረተ ሥጋቸውን ገላልጠው የሄዱትና በዕድሜ ሲገፉ ወደማንነታቸው የተመለሱት ሳይሆኑ : ማንነታቸውን በወጣትነታቸው ዘመን ሳይረሱ ሙዝየሞቻቸውን : ትምህርት ቤቶቻቸውን : ዩኒቨርስቲዎቻቸውን : የጦር ሰፈሮቻቸውን : ላቦራቶሪዎቻቸውን ቀጥ አድርገው ገትረው የያዙ ሰዎች ናቸው :: እነዚሁ ወገኖች ናቸው የካውንስሊንግ ተቋማት ከፍተው : እነዚህኑ ማንነታቸው የጠፋባቸውን ሰዎች እያከሙ ወደማንነታቸው የሚመልሱዋቸው :: ለዛ ነው 10% በሚሰራው ነው 90%ቱ የሚዝናናው ማለት ደረጃ የደረሱት ::
Quote: ይልቅስ ስር ከያዘ የማይነቀለውን ሌላ የባዕድ ባህል ነው ማውገዝ ::
ስፔሲፊካሊ ምን ምን ናቸው እነዚህ የማይነቀሉ ሥር የሰደዱ የሌሎች ባሕሎች ? ዘርዝርልኝ !
Quote: ይሄ በረባ ባልረባ ታዳጊዎችን መኮነን ለእኔ ትምክህተኝነት ነው ::
ኦው ! መለስ ዜናዊ ሊሆን ነዋ የትምክህተኞች ቁንጮ !!
ታዳጊዎችን "አደገኛ ቦዘኔ " እያለ "ሽብርተኛ " እያለ " አመጸኛ " እያለ : የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ሳይቀር ደዴሳ ወስዶ በወባ እየጠበሰ : በክረምት በፕሮፓጋንዳ እያቀወሰ : በየተቋማቱ የብሔር ግጭት ሲነሳ የትግራይን ታዳጊዎች እያሰለጠነ ሰላይና ጆሮ ጠቢ እያደረገ ብዙዎችን ሪከርዳቸውን ያበላሸና ከአገርም ወጥተው እንዲሰደዱ ያደረገ ...... ይሄው መለስ ዜናዊ ነዋ ትምክህተኛው !!!
Quote: ... እኔ የማዳምጠው ዘለሰኛ : የምወርደው እስክስታ ወይም የምለብሰው የክት ልብስ ብቻ ነው ትክክል ማለት ተመጻዳቂ መሆን ብቻ ነው ትርፉ :: አይመስልህ ?
ሓየት
አዳፕት የሚለው ቋንቋ ትርጉሙን ታውቀዋለህ ? እርሱ ቢገባህ እንዲህ ብለህ የደደብ አስተያየት አትሰጥም ነበር !
በጸባይ ያዋራሁህ ደኅና ሰው መስለኸኝ ነበር ::
አንተ ራስህ ሸለምጥማጥ ነህ ! ወያኔ !!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ናፖሊዮን ዳኘ Joined: 18 Apr 2008 Posts: 1874
Posted: Wed Apr 18, 2012 4:33 am Post subject:
Quote: የሰለጠነውን ዓለም የሰለጠነ ያደረጉት እነዚህ ሐፍረተ ሥጋቸውን ገላልጠው የሄዱትና በዕድሜ ሲገፉ ወደማንነታቸው የተመለሱት ሳይሆኑ : ማንነታቸውን በወጣትነታቸው ዘመን ሳይረሱ ሙዝየሞቻቸውን : ትምህርት ቤቶቻቸውን : ዩኒቨርስቲዎቻቸውን : የጦር ሰፈሮቻቸውን : ላቦራቶሪዎቻቸውን ቀጥ አድርገው ገትረው የያዙ ሰዎች ናቸው :: እነዚሁ ወገኖች ናቸው የካውንስሊንግ ተቋማት ከፍተው : እነዚህኑ ማንነታቸው የጠፋባቸውን ሰዎች እያከሙ ወደማንነታቸው የሚመልሱዋቸው :: ለዛ ነው 10% በሚሰራው ነው 90%ቱ የሚዝናናው ማለት ደረጃ የደረሱት ::
you rock! እንዳንተ አይነት ነገሩ የገባው ሰው ነው ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት !
እግዜር ቁጥራችሁን ያብዛው :: ሌላ ምን ይባላል :: _________________ ሰው ህሊናውን የሚሸጠው ክህሊና በላይ ዋጋ ያለው ምን ነገር ሊገዛበት ነው?
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ፕላዞግ Joined: 06 Dec 2008 Posts: 31
Posted: Wed Apr 18, 2012 6:55 am Post subject:
ሀገርኛው ከውጭው ስልት ጋር በጥሩ ባለሙያዎች ተዋሀደና ደስ የሚል ስራ ተሰራ :: ካሁን በፊት 'ጉራጌ ቶን ' ብለው እንደሰሩት ወጣቶች እነዚህም የሚደነቁ እና በርቱ የሚባሉ ናቸው :: ሓየት የተናገረው የሚበረታታ እና የሚወገዝ ነገር እንለይ ነው ...ባጭሩ ! እሱ ለተናገረው ቃል በቃል መልስ ለመስጠት ሲሞከር አይቼ ...ጎበዝ ስራ የለም እንዴ ! አላልኩም ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ሓየት 11 Joined: 06 Apr 2008 Posts: 2735 Location: ላን'ሊይ
Posted: Wed Apr 18, 2012 12:14 pm Post subject:
አይተ አመሰግናለሁ
ቅሌታም ዲያቆን ነህ እንዴ ሰው ሳይደርስብህ መድረስ ብልግና አይደለም ዎይ የደደቡ ናቦ ጠበቃ ሆነህ ... ደደብ አልከኝ ቅቅቅቅ ወይ ልክን አለማወቅ ... ሓየት ማለት ማን እንደሆነ ማን በነገረህ አንት አዛባ ... በተካንኩበት የማንቆራጠጥ ሙያዬ አሳይህ ነበር ... ግን ምን ይሁን ... ለዛሬ ይለፈኝ ...
በል ይቺን ደግመህ በደንብ አላምጣትና ድቁናህ ላይ በርታ ... ሌላ ሌላውን ለእኛ ጊዜውን ቀድመን ለምንገኝ .. ከጊዜያችን በፊት ቀድመን ለተወለድነው ለአዋቂዎቹ ተወልን ...
ሱሪ ዝቅ አድርገው መልበሳቸው ግርምት ፈጠረብህ አይደል ... ሱሪው ራሱ እኮ ያንተ ባህል አልነበርም ... ይሄኔ ያገለደምከውን ጨርቅ ገለብ አድርገህ ነበር ... እንደውሻ አጥር ተደግፈህ የምትሸናው
ሓየት
ካልተወለዱት _________________ An eye for an eye, and the whole world would be blind. (KGK)
>>>>>>>>> ገዛ ሓየት
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እናመሰግንሃለ Joined: 01 Jun 2009 Posts: 805
Posted: Wed Apr 18, 2012 3:52 pm Post subject:
ፕላዞግ እንደጻፈ(ች)ው : ሀገርኛው ከውጭው ስልት ጋር በጥሩ ባለሙያዎች ተዋሀደና ደስ የሚል ስራ ተሰራ :: ካሁን በፊት 'ጉራጌ ቶን ' ብለው እንደሰሩት ወጣቶች እነዚህም የሚደነቁ እና በርቱ የሚባሉ ናቸው :: ሓየት የተናገረው የሚበረታታ እና የሚወገዝ ነገር እንለይ ነው ...ባጭሩ ! እሱ ለተናገረው ቃል በቃል መልስ ለመስጠት ሲሞከር አይቼ ...ጎበዝ ስራ የለም እንዴ ! አላልኩም ::
ፕላዞግ :
ሓየትና ናፖልዮን ሁሌ ጥሩ ጥሩ ነጥቦች የሚያነሱ ጸሐፊዎች ናቸው ብዬ ስለማምን (ሓየትን ብዙም በቅርበት ባላነበውም ) ከዚህ በፊት ልገላግላቸው እሞክር ነበር :: ሓየትን በተለይ አስተያየትህ ፐርሰናል አይሁን እለው ነበር :: ያሁኑም የመጀመርያ ሙከራዬ ይሄ ነበር :: ከላይ እንደጠቀስኩት የሙዚቃ ባለሙያዎችን ራሱ እያሳሰባቸው የመጣውን ጉዳይ ምንም ችግር የለውም ብሎ መካድ የትም አያደርስም :: (መቼም ሕዝብ አይታመንም አይደል ?)
ሓየት ለመጀመሪያው ፖስቴ የሰጠኝ መልስ ግን ከጉዳዩ ይልቅ ሓየት አመለካከት ላይ ያለኝን ኢንተረስት ነው ጨመረው :: እንደምታየው መልሱን አንድ በአንድ አናላይዝ አደረግሁና እልም ያለ ወያኔ ሆኖ አገኘሁት :: እስቲ አሁን ቻቺን አፉን ሞልቶ "በሕዝብ የተወደሰች " ይለኛል ?!!! ይሄ ደደብ ?!!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ሓየት 11 Joined: 06 Apr 2008 Posts: 2735 Location: ላን'ሊይ
Posted: Wed Apr 18, 2012 4:48 pm Post subject:
ከውሻ ጋር ስትጋፋ ስላደግክ የውሻ ባህሪ ለብሰህ እንጂ ... መሬት ጠብ የማይል እውነታ ነው የጻፍኩት - መጀመሪያም ቢሆን መጨረሻ :: ለነገር የመጣ ሰው ግን ምንም አይመልሰውምና ይህን ግማታም አፍህን ከፍተህብኝ ሄድክ :: ሰው በማያገባው ገብቶ እንዴት ይቀላል አንተን ብሎ ደግሞ ሽማግሌ ሲሉ ሰምትሀል ... ድንጋይ ራስ
የፈለጋችሁትን ሁኑ ... ሰማይ ደርሳችሁ መሬት ለምን አትፈርጡም ... ዛሬ ከሀ እስከ ፈ (ፐ አልልም አንዳንድ ስለሚኖሩ ) ድረስ ያሉት ዘመናዊ ዘፈኖች በብዙ መልኩ ከውጪ የተወረሱ ናቸው :: ... ደደብ ጭንቅላትህን አለቦታው ከምታስገባ ... የሚወገዝ አውግዝ :: በሰው ምርጫ ደግሞ ምንም አያገባህም :: በተመቻቸው ስልት ዘፈኑ ... ትላንት እነ ቻቺ , አስቴር , አለማየሁ እሸቴ , ወዘተ እንደዘፈኑት ሁሉ ... ዛሬም ነገም እንዲህ ቀያይጠው የሚዘፍኑ ... የሙዚቃውን ኢንዱስትሪ የሚያሳድጉ ... በአለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የሚሆኑ ... አርቲስቶች ይኖራሉ :: ላንተ አይነቱ ውቅር ደደብ ሲባል ... ዘለሰኛና ማሲንቆ ብቻ እየተዘፈነ , በገና ብቻ እየተደረደረ , አይኖርም :: አራት ነጥብ ::
ሓየት
እናመሰግንሃለ� እንደጻፈ(ች)ው : ፕላዞግ እንደጻፈ(ች)ው : ሀገርኛው ከውጭው ስልት ጋር በጥሩ ባለሙያዎች ተዋሀደና ደስ የሚል ስራ ተሰራ :: ካሁን በፊት 'ጉራጌ ቶን ' ብለው እንደሰሩት ወጣቶች እነዚህም የሚደነቁ እና በርቱ የሚባሉ ናቸው :: ሓየት የተናገረው የሚበረታታ እና የሚወገዝ ነገር እንለይ ነው ...ባጭሩ ! እሱ ለተናገረው ቃል በቃል መልስ ለመስጠት ሲሞከር አይቼ ...ጎበዝ ስራ የለም እንዴ ! አላልኩም ::
ፕላዞግ :
ሓየትና ናፖልዮን ሁሌ ጥሩ ጥሩ ነጥቦች የሚያነሱ ጸሐፊዎች ናቸው ብዬ ስለማምን (ሓየትን ብዙም በቅርበት ባላነበውም ) ከዚህ በፊት ልገላግላቸው እሞክር ነበር :: ሓየትን በተለይ አስተያየትህ ፐርሰናል አይሁን እለው ነበር :: ያሁኑም የመጀመርያ ሙከራዬ ይሄ ነበር :: ከላይ እንደጠቀስኩት የሙዚቃ ባለሙያዎችን ራሱ እያሳሰባቸው የመጣውን ጉዳይ ምንም ችግር የለውም ብሎ መካድ የትም አያደርስም :: (መቼም ሕዝብ አይታመንም አይደል ?)
ሓየት ለመጀመሪያው ፖስቴ የሰጠኝ መልስ ግን ከጉዳዩ ይልቅ ሓየት አመለካከት ላይ ያለኝን ኢንተረስት ነው ጨመረው :: እንደምታየው መልሱን አንድ በአንድ አናላይዝ አደረግሁና እልም ያለ ወያኔ ሆኖ አገኘሁት :: እስቲ አሁን ቻቺን አፉን ሞልቶ "በሕዝብ የተወደሰች " ይለኛል ?!!! ይሄ ደደብ ?!!
_________________ An eye for an eye, and the whole world would be blind. (KGK)
>>>>>>>>> ገዛ ሓየት
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እናመሰግንሃለ Joined: 01 Jun 2009 Posts: 805
Posted: Wed Apr 18, 2012 5:00 pm Post subject:
ሓየት 11 እንደጻፈ(ች)ው : ... ትላንት እነ ቻቺ , አስቴር , አለማየሁ እሸቴ , ወዘተ እንደዘፈኑት ሁሉ ... ዛሬም ነገም እንዲህ ቀያይጠው የሚዘፍኑ ... የሙዚቃውን ኢንዱስትሪ የሚያሳድጉ ... በአለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የሚሆኑ ... አርቲስቶች ይኖራሉ :: ላንተ አይነቱ ውቅር ደደብ ሲባል ... ዘለሰኛና ማሲንቆ ብቻ እየተዘፈነ , በገና ብቻ እየተደረደረ , አይኖርም :: አራት ነጥብ ::
ውይ በሞትኩት ! እኔ 'ኮ ቻቺን መለስ ያወደሳት ጎዳና ተዳዳሪዎችን ስለረዳች ይመስለኝ ነበር :: ለካ በአለማቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ ስለሆነችና ዘለሰኛና መሰንቆ ስለማትደረድር ነው ?!! ቅቅቅቅቅቅ ......!!!!
ሱሪን ዝቅ አድርጎ መልበስን ከመሰንቆና ዘለሰኛ ጋር ማገናኘትህ ደግሞ ደደብነትህን ያሳያል :: ናፖልዮን ጊታሩን ወይም ኦርጋኑን ተቃውሞ አልነበረም 'ኮ ቤቱን የከፈተው ?!! አይ ወያኔ ! የተጻፈውን በትክክል አንብበህ ተረዳ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
ሓየት 11 Joined: 06 Apr 2008 Posts: 2735 Location: ላን'ሊይ
Posted: Wed Apr 18, 2012 5:34 pm Post subject:
እናመሰግንሃለ� እንደጻፈ(ች)ው :
ሱሪን ዝቅ አድርጎ መልበስን ከመሰንቆና ዘለሰኛ ጋር ማገናኘትህ ደግሞ ደደብነትህን ያሳያል :: ናፖልዮን ጊታሩን ወይም ኦርጋኑን ተቃውሞ አልነበረም 'ኮ ቤቱን የከፈተው ?!! አይ ወያኔ ! የተጻፈውን በትክክል አንብበህ ተረዳ ::
ቅቅቅ ያለቦታህ እንደውሻ መልከስከስ አያምርብህም አልኩህ እኮ ::
በመጀመሪያ የተቃወመው ብኋላም ለመረረው ሲመልስለት በግልጽ እንዳስቀመጠው ጎንደርኛውን ለምን ከውጪ ጋር ቀላቅቀሉት ነው :: እኔ ደግሞ ከላይ የማወራው ዘመናዊ የሚባለው ዘፈን በሙሉ የቅልቅል ውጤት ነው ነው :: ባይቀላቀልማ ከበገና , ክራር ማሲንቆ , ከበሮ ወዘተ አትወጣም ነበር :: አሁን ጊታርን የማትቃወመው እኮ ከኛ ጋር ስለተዋሀደና አዳፕት ስላደረግከው አይደለም እንዴ አሁን ፎርግራንትድ የምትወስደው ልክ ያንተ እንደሆነ ያህል ስለተለማድከው አይደለም ዎይ ልቃወም ብትልም ምንም ማድርገ እንደማትችል ታውቀዋለህ :: ዛሬ አንተም ሆንክ ደደቡ አቻህ የምታወግዙት የቅይጥ ስልት ... ከኛና ከባህላችን ጋር እስኪዋሀድ ድረስ ነው :: ከዛ ብኋላማ ልክ ዛሬ ቦላሌ ማጥለቅ ኖርማል እንደሆነው ሁሉ ቅይጥ ዘፈኖችም ፎር ግራንትድ ትወስዳቸዋለህ :: ቴዲ አፍሮ እንዲህ ዛሬ ፊዮሪና ብሎ ስለዘፈን ጉድ ሊባል "ጃ ያስተሰርያል " ሲል ጀግና ትሉት ነበር እንጂ የሙዚቃ ባህላችንን አረከሰው ወይም አጠፋው ስትሉ አልሰማንም :: ዛሬ ግን ቴዲ አፍሮ ብትል ጎሳዬ , ሽዋንዳኝ ብትል ጥበቡ ወርቅዬ , ዘሪቱ ብትል ጸደኒያ , አስቴር ብትል ወላ ጂጂ ... ወዘተ ማን ነው ከውጪ ጋር ሳያዳቅል የሚዘፍን ህዝብም ይኸው የሙዚቃ ስሜቱን ለማርካት ከዘለሰኛው ጎን አብሮ ይገዛዋል :: እንደጉድ ያዳምጠዋል :: የናንተ ውግዘት ሳይሆን የህዝቡ ዲማንድና የአርቲስቶቹ የፈጠራ ብቃት ነው የሚወስነው :: ልፋ ሲልህ ግን ይህን ቀዳዳ አፍህን ለመክፈት ስትንደረደር መጣህ እንጂ ::
ሱሪውም ቢሆን ይጠቅማል ካለና አመዛኙ ማህበረሰብ ከተቀበለው ዝቅ ተደርጎ ይለበሳል :: ልክ ብጣሽ ጨርቅ ከማገልደም ወደ ቦላሌ እንደተለወጥከው ማለት ነው ::
አሁንም ደግሜ ነው የምንገርህ ... የሚወገዘውን አውግዝ :: በተለይ ደግሞ ከማውገዝህ በፊት የሚጠበቅብህን በቅድሚያ ተወጣ :: በቅድሚያ ባህልህን ጠንቅቀህ እወቅና ባህልህን እንዳያስነጥቁህ ለምትሰጋባቸው ታዳጊዎች አስጠና :: ዝም ብሎ የደነዝ ሰው ተቃውሞ ከዋርካ አያልፍም :: በተለይ ደግሞ ጽንፈኛ ኮንዘርቫቲቭዝም ለማንም እንደማይጠቅም መረዳት ይኖርብሀል ::
አለቃ ሓየት
ስረ መሰረቱን ያልለቀቀው _________________ An eye for an eye, and the whole world would be blind. (KGK)
>>>>>>>>> ገዛ ሓየት
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator
እናመሰግንሃለ Joined: 01 Jun 2009 Posts: 805
Posted: Wed Apr 18, 2012 5:51 pm Post subject:
ሓየት 11 እንደጻፈ(ች)ው :
በመጀመሪያ የተቃወመው ብኋላም ለመረረው ሲመልስለት በግልጽ እንዳስቀመጠው ጎንደርኛውን ለምን ከውጪ ጋር ቀላቅቀሉት ነው :: እኔ ደግሞ ከላይ የማወራው ዘመናዊ የሚባለው ዘፈን በሙሉ የቅልቅል ውጤት ነው ነው :: ባይቀላቀልማ ከበገና , ክራር ማሲንቆ , ከበሮ ወዘተ አትወጣም ነበር :: ......ልቃወም ብትልም ምንም ማድርገ እንደማትችል ታውቀዋለህ ::
አዳፕት ማድረግ ማለት ምን ማለት ነው ? የሚለውን ቀደም ብዬ ያስቀመጥኩልህን ጥያቄ ብትመልስ ኖሮ እንዲህ አትዋከብም ነበር :: የኢትዮጵያውን ቢት ለማሳደግ በውጭ መሳርያ ወይም የሙዚቃ አካሄድ መጠቀም ? ወይስ የውጭውን አስገብቶ የአገር ውስጡን ለማጥፋት በማሰብ ለሕዝቡ መሳቢያና ለጊዜው እንዲዋጥለት ብቻ ባሕላዊውን እንደጨው በላዩ ላይ ጣል በማድረግ የውጭውን መጋት ?
የእኔ የግል አስተያየት እንዳውም እነዚህ ዘመናይ ነን ባዮች የሚያወጡት ላይ ሳይሆን ባሕላዊ ተብለው የሚወጡት ላይ ነው የሚጀምረው :: አንተ ደንቆሮ ስለሆንክ ላንተ አይነገርህም እንጂ ባሕላዊ ሙዚቃዎች እንዲያስጠሉ ሆን ተብለው የሚደረጉ የግሎባላይዜሽንና የግሎካላይዜሽን ድሪቶዎች በየሙዚቃ ክሊፑ አሉ ::
ጽንፈኛ ኮንሰርቫቲቪዝም ትላለህ :: ደደብ ! ስንት ሺህ ወጣቶች ባሁን ዘመን ኦርጋኑም ዘፈኑም ይቅርብኝ ብለው ራሳቸውን በበገናና ዘለሰኛ ከወሰኑና ወደፈጣሪያቸው ከተመለሱ ሰንበትበት ብለዋል :: ልቃወም ብትልም ምንም ማድረግ አትችልም ላልከው ከመቻልማ ታልፎ ይኸው ውጤቱ ታየ ! አያ መለስ ይደንብር እንጂ እውነታው ያ ነው !
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
toolbar creator