WARKA Forum Index  
 FAQFAQ   SearchSearch   MemberlistMemberlist   UsergroupsUsergroups   RegisterRegister 
 ProfileProfile   Log in to check your private messagesLog in to check your private messages   Log inLog in 

ዋርካ ቻት - በአማርኛ በቀጥታ ይወያዩ! Warka Live Chat | Home (New!) | About us | Contact us
ኢትዮጵያ - በወያኔዎች ለሽያጭ የቀረበች አገር
Goto page Previous  1, 2, 3, 4 ... 13, 14, 15  Next
 
Post new topic   Reply to topic    WARKA Forum Index -> Warka Politics - ዋርካ ፖለቲካ


 
View previous topic :: View next topic  
Author Message
ኣሲምባ

ዋና ኮትኳች


Joined: 12 Oct 2006
Posts: 527

PostPosted: Thu Apr 08, 2010 12:34 am    Post subject: Reply with quote

የድሬው - የከዚራው - ገንደቆሬ ገንደምስኪን - ለገሀሬ - -አፈጢሳ - - ሳቢያን - - ግሪክ ካምፕ - - ደቻቱ - - መጋላ - -ቀፊራ - - አዲስ ከተማ ?
ታጨሮ - - ረብሳ - - ምናምን ትፈለጋልህ ?
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Thu Apr 08, 2010 4:17 pm    Post subject: Reply with quote

ሰላም ወገኖቼ :-

አዲሶቹ ቅኝ ገዢዎች ቻይናና ሕንድ በአፍሪቃ እና በኢኮኖሚ ባልበለጽጉት አገሮች የሚያደርጉት የመሬት ግዢ ሽሚያ ገደብ ያጣና ምናልባትም 21ኛው ክፍለ -ዘመንን የዓለማችንን የፖለቲካ አቅጣጫ የሚወስን ሊሆን ይችላል :: ለምሣሌ ሕንዶች ከወያኔ ጋር በሚያደርጉት የመሬት ግዢ ምን ያህል ገንዘብ አውጥተዋል ? ምን ያህል መሬትስ ወስደዋል ? በቅርቡ ራውል ጎስዋሚ የተባለ አንድ የሕንድ ጋዜጠኛ ያቀረበውን ዘገባ ተመልከቱት ::

Quote:
Ethiopia: The then Ambassador of Ethiopia has sought clarification from the RBI regarding opportunities for Indian investors for land-buying in Ethiopia. Ambassador was of the view that India has been leading the land-buying race with investments now standing at US$ 4.3 billion. However, the RBI has informed that as per its records, the total amount invested in Ethiopia from 1960 to the end of July 2009 by residents in India by way of overseas direct investments is only US$ 9.3 million towards equity. It is clear that there exists immense opportunities for leasing of land by Indian companies/farmers.

...
In Ethiopia, the government of former Marxist rebels that had once promised land to the tiller has set aside more than 2.5 million hectares for agri-business. Global investors are lured with 40-year leases and tax holidays by a regime desperate for foreign currency. The Ethiopian Review, a current affairs magazine, has reported that Indian companies have committed US$ 4.2 billion to agri-investment in Ethiopia (the figure matches the contested number in the summary issued by the Ministry of Agriculture). Karuturi Agro Products farms 12,000 hectares in Ethiopia and grows corn on smallholder land which once supported teff, a local foodgrain. Hundreds of Ethiopian workers, overseen by Indian supervisors, were bent over rows of corn stalks, cutting weeds tangled around them with small blades, reported The Ethiopian Review. Many of the workers were children. The day rate: 8 birr, about 70 cents. Ethiopians cannot own land, instead they hold use certificates for their tiny plots, making it difficult to get loans, or to sell or increase holdings. A worker said the company had refused to sign a wage contract and had failed to deliver promised water and power to nearby villages. Supervisors treat them cruelly, he said, and most workers were just biding time until they could go work for a Chinese construction company rumoured to pay US$ 2-4 a day. The Review said that India dominates foreign direct investment in the agricultural sector with investment in place of US$ 2.1 billion, followed by the EU (US$ 1.44 billion), the USA (US$ 542 million), Israel (US$ 528 million) and Saudi Arabia (US$ 172 million).

The international rush to farm Ethiopian land has prompted media attention worldwide on what is now called the 21st century land grab. In an investigation published on March 7, 2010, by the British weekly newspaper, The Observer, conditions in a region called Oromia are described. Oromia is one of the centres of the African land rush, said the Observer report. Haile Hirpa, president of the Oromia studies association, said last week in a letter of protest to UN Secretary General Ban Ki-Moon that India had acquired 1 million hectares, Djibouti 10,000 hectares, Saudi Arabia 100,000 hectares, and that Egyptian, South Korean, Chinese, Nigerian and other Arab investors were all active in the state.


ሕንዶች እስከ 4.3 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚያካሂዱት የመሬት ግዢ እና ኢንቨስትመንት አውለዋል :: ይህ ኢንቨስትመንት ከወያኔ ጋር በቀጥታ በሚደረግ ድርድር የተከናወነ በመሆኑ ትክክለኛ የገንዘቡ መጠን ከዚህ ከተጠቀሰው ገንዘብ 30% የበለጠ እንደሚሆን መገመት ይቻላል (ለወያኔ ቡችሎች የሚከፈል ጉቦ ተጨምሮበት ) :: እንግዲህ ሃቁ ይህን ይመስላል ::

ምንጭ :- Rahul Goswami, April 5, 2010. African landrush

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ቢተወደድ

ዋና ውሃ አጠጪ


Joined: 21 Jul 2009
Posts: 1554
Location: Dabra Za`Yet

PostPosted: Fri Apr 09, 2010 8:30 am    Post subject: Reply with quote

ተላ እስቲ ባገራችን ምሁር የታጻፈ አምጣና አስነብበን :: እስከመቼ ድረስ ውድቀታችንን ለሚመኙ ባእዳን ነጋሪት ትጎሽማለህ ?

የኛው ችግር መፈታት አለበት በኛው ::


ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው:
ሰላም ወገኖቼ :-

አዲሶቹ ቅኝ ገዢዎች ቻይናና ሕንድ በአፍሪቃ እና በኢኮኖሚ ባልበለጽጉት አገሮች የሚያደርጉት የመሬት ግዢ ሽሚያ ገደብ ያጣና ምናልባትም 21ኛው ክፍለ -ዘመንን የዓለማችንን የፖለቲካ አቅጣጫ የሚወስን ሊሆን ይችላል :: ለምሣሌ ሕንዶች ከወያኔ ጋር በሚያደርጉት የመሬት ግዢ ምን ያህል ገንዘብ አውጥተዋል ? ምን ያህል መሬትስ ወስደዋል ? በቅርቡ ራውል ጎስዋሚ የተባለ አንድ የሕንድ ጋዜጠኛ ያቀረበውን ዘገባ ተመልከቱት ::

Quote:
Ethiopia: The then Ambassador of Ethiopia has sought clarification from the RBI regarding opportunities for Indian investors for land-buying in Ethiopia. Ambassador was of the view that India has been leading the land-buying race with investments now standing at US$ 4.3 billion. However, the RBI has informed that as per its records, the total amount invested in Ethiopia from 1960 to the end of July 2009 by residents in India by way of overseas direct investments is only US$ 9.3 million towards equity. It is clear that there exists immense opportunities for leasing of land by Indian companies/farmers.

...
In Ethiopia, the government of former Marxist rebels that had once promised land to the tiller has set aside more than 2.5 million hectares for agri-business. Global investors are lured with 40-year leases and tax holidays by a regime desperate for foreign currency. The Ethiopian Review, a current affairs magazine, has reported that Indian companies have committed US$ 4.2 billion to agri-investment in Ethiopia (the figure matches the contested number in the summary issued by the Ministry of Agriculture). Karuturi Agro Products farms 12,000 hectares in Ethiopia and grows corn on smallholder land which once supported teff, a local foodgrain. Hundreds of Ethiopian workers, overseen by Indian supervisors, were bent over rows of corn stalks, cutting weeds tangled around them with small blades, reported The Ethiopian Review. Many of the workers were children. The day rate: 8 birr, about 70 cents. Ethiopians cannot own land, instead they hold use certificates for their tiny plots, making it difficult to get loans, or to sell or increase holdings. A worker said the company had refused to sign a wage contract and had failed to deliver promised water and power to nearby villages. Supervisors treat them cruelly, he said, and most workers were just biding time until they could go work for a Chinese construction company rumoured to pay US$ 2-4 a day. The Review said that India dominates foreign direct investment in the agricultural sector with investment in place of US$ 2.1 billion, followed by the EU (US$ 1.44 billion), the USA (US$ 542 million), Israel (US$ 528 million) and Saudi Arabia (US$ 172 million).

The international rush to farm Ethiopian land has prompted media attention worldwide on what is now called the 21st century land grab. In an investigation published on March 7, 2010, by the British weekly newspaper, The Observer, conditions in a region called Oromia are described. Oromia is one of the centres of the African land rush, said the Observer report. Haile Hirpa, president of the Oromia studies association, said last week in a letter of protest to UN Secretary General Ban Ki-Moon that India had acquired 1 million hectares, Djibouti 10,000 hectares, Saudi Arabia 100,000 hectares, and that Egyptian, South Korean, Chinese, Nigerian and other Arab investors were all active in the state.


ሕንዶች እስከ 4.3 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚያካሂዱት የመሬት ግዢ እና ኢንቨስትመንት አውለዋል :: ይህ ኢንቨስትመንት ከወያኔ ጋር በቀጥታ በሚደረግ ድርድር የተከናወነ በመሆኑ ትክክለኛ የገንዘቡ መጠን ከዚህ ከተጠቀሰው ገንዘብ 30% የበለጠ እንደሚሆን መገመት ይቻላል (ለወያኔ ቡችሎች የሚከፈል ጉቦ ተጨምሮበት ) :: እንግዲህ ሃቁ ይህን ይመስላል ::

ምንጭ :- Rahul Goswami, April 5, 2010. African landrush

ተድላ

_________________
When we do it right No-one remembers,
When we do it wrong No-one forgets.
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Send e-mail Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Fri Apr 09, 2010 4:42 pm    Post subject: Reply with quote

ቢተወደድ እንደጻፈ(ች)ው:
ተላ እስቲ ባገራችን ምሁር የታጻፈ አምጣና አስነብበን :: እስከመቼ ድረስ ውድቀታችንን ለሚመኙ ባእዳን ነጋሪት ትጎሽማለህ ?

የኛው ችግር መፈታት አለበት በኛው ::


አንተ ወያኔ እንጂ ኢትዮጵያዊ አይደለህም :: ስለዚህ እኔ ኢትዮጵያዊው ካንተ ጋር እኩል ተቆጥሬ "እኛ " ብለህ ልትጠራኝ አትችልም ::

በገሃድ እና በኅሊና ያሠራችኋቸውን : ከፈቃዳቸው ውጪ ከአገራቸው እንዲሠደዱ ያደረጋችኋቸው አያሌ ኢትዮያውያን ምሁራን የሚሉትን ለማዳመጥ ጆሮውም : የሚጽፉትን ለማንበብና ለማገናዘብ ኅሊናው የላችሁም :: ስለዚህ ጌቶቻችሁ ፈረንጆች : ቻይኖች : ሕንዶች እና አረቦች የሚጽፉትን እያመጣን እናስነብባችኋለን ::

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Fri Apr 09, 2010 11:46 pm    Post subject: Reply with quote

ሰላም ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ :-

ሣህሌ (ስዬ ) አብርሃ የተቻለውን ያህል ከለገሠ (መለስ ) የተሻለ ኦሪጅናል ወያኔ መሆኑን ለማሥመስከር ብቻ ሣይሆን በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተሻለ ሰው ሆኖ ለመታዬት እየጣረ ነው :: ስለ ወያኔና የሱዳን እስላማዊ አገዛዝ ይህንን ብሏል ::

Quote:
ኢህአዴግ ከሕዝብ በስተጀርባ የኢትዮ -ሱዳንን ድንበር ለማካለል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጥብቆ ይቃወማል፡፡

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሱዳን መልካም ግኑኝነት እንዲኖራት የመድረክ ፍላጎት እና እምነት ቢሆንም በኢትዮጵያ ሉኣላዊ መሬት ዋጋ እንዲሆን አይፈቅድም፡፡


ምንጭ :- አቡጊዳ : የባሕር በር አስፈላጊነትን አስምሮበት ከሱዳን ጋር በድብቅ የሚደረገዉን ስምምነት፣ የሶማሊያን ጦርነት መድረኩ አወገዘ

ቢያንስ አንድ ወያኔ ከሱዳን እስላማዊ አገዛዝ ጋር ኢትዮጵያን የሚጎዳ የሚሥጢር ድርድር እየተደረገ መሆኑን አምኗል ::

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ክቡራን

ዋና አለቃ


Joined: 04 Mar 2008
Posts: 4372

PostPosted: Sat Apr 10, 2010 1:03 am    Post subject: Reply with quote

ሰላም ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ::
መርዘኝነትንና መለያየትን በመካከላችን የሚረጩትን መንጠቆዎች ለይተን እናውጣ :: "ወገኖቼ " እያለ ልባችንን ሊበላን አእምሯችን ሊነጥቀን ከሚሞክር ነጣቂ ተኩላ ራሳችንን እንጠብቅ :: "ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ " እያሉ የሚያማልሉ ቃላቶች እየመረጡ የሚጽፉልንን ሰው መሳይ በሽንጎዎች ማንነት እንመርመር :: ምንም ውጫቸውን በተብለጨለጨ የስጦታ መጠቅለያ ወረቀት ጠቅልለው ቢያቀርቡልንም በመርዛቸው እንዳንነደፍ ተጠንቅቀን አካሄዳቸውን እናጢን እንገምግም :: ኢትዮጵያውነት የግብር እዳ እንጂ የቃላት ሰልፍ አይደለም :: ኢትዮጵያውነት ያንድነት የፍቅር ማያያዣ ሸማ እንጂ የማከፋፈያ ድማሚት አይደለም :: ኢትዮጵያዊነት በምርጥ ቃላት የምንሸነጋገልበት የቃላት በትር ሳይሆን የተግባር አውድ ነው :: ኢትዮጵያዊነት እንደ ቡሄ ዳቦ እያለሳለሱ ሊበሉት የሚዞሩት ሽልጦ ሳይሆን የትስስር የመስዋእትነት የፍቅር አጥር ነው :: ኢትዮጵያዊነት ገድል ነው :: ኢትዮጵያዊነት ባአንድ በራሱ ሰርቶ መቆም ባልቻለ በዌል ፌር ተዳዳሪ ተልክቶ የሚሰጥ ሳይሆን የአያት የቅድም አያት ውርስ ነው :: "ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ " እያለ በማር የተለወሰ መርዝ ሊያቀምሰን የሚሞክር በቃላት የሞከተ በተግባር ግን የተሰለበ ስልብ ማንነትና ምንነት አንጥረንና አንጠርጥረን እንወቅ :: እንመርምር :: የሚያብለጨልጭ ሁሉ ወርቅ አይደለም ::
ክቡራን ነኝ :: የተደበቁ መርዛማ እባቦችን ከሚመነጥሩ ወገኖች ጎራ ::
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Visit poster's website Report post
መቅደላዊ

ዋና ኮትኳች


Joined: 01 Dec 2009
Posts: 599
Location: Ethiopia

PostPosted: Sat Apr 10, 2010 10:33 am    Post subject: Reply with quote

ክቡራን እንደጻፈ(ች)ው:
ሰላም ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ::
መርዘኝነትንና መለያየትን በመካከላችን የሚረጩትን መንጠቆዎች ለይተን እናውጣ :: "ወገኖቼ " እያለ ልባችንን ሊበላን አእምሯችን ሊነጥቀን ከሚሞክር ነጣቂ ተኩላ ራሳችንን እንጠብቅ :: "ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ " እያሉ የሚያማልሉ ቃላቶች እየመረጡ የሚጽፉልንን ሰው መሳይ በሽንጎዎች ማንነት እንመርመር :: ምንም ውጫቸውን በተብለጨለጨ የስጦታ መጠቅለያ ወረቀት ጠቅልለው ቢያቀርቡልንም በመርዛቸው እንዳንነደፍ ተጠንቅቀን አካሄዳቸውን እናጢን እንገምግም :: ኢትዮጵያውነት የግብር እዳ እንጂ የቃላት ሰልፍ አይደለም :: ኢትዮጵያውነት ያንድነት የፍቅር ማያያዣ ሸማ እንጂ የማከፋፈያ ድማሚት አይደለም :: ኢትዮጵያዊነት በምርጥ ቃላት የምንሸነጋገልበት የቃላት በትር ሳይሆን የተግባር አውድ ነው :: ኢትዮጵያዊነት እንደ ቡሄ ዳቦ እያለሳለሱ ሊበሉት የሚዞሩት ሽልጦ ሳይሆን የትስስር የመስዋእትነት የፍቅር አጥር ነው :: ኢትዮጵያዊነት ገድል ነው :: ኢትዮጵያዊነት ባአንድ በራሱ ሰርቶ መቆም ባልቻለ በዌል ፌር ተዳዳሪ ተልክቶ የሚሰጥ ሳይሆን የአያት የቅድም አያት ውርስ ነው :: "ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ " እያለ በማር የተለወሰ መርዝ ሊያቀምሰን የሚሞክር በቃላት የሞከተ በተግባር ግን የተሰለበ ስልብ ማንነትና ምንነት አንጥረንና አንጠርጥረን እንወቅ :: እንመርምር :: የሚያብለጨልጭ ሁሉ ወርቅ አይደለም ::
ክቡራን ነኝ :: የተደበቁ መርዛማ እባቦችን ከሚመነጥሩ ወገኖች ጎራ ::


አንተ ነህ ኢትዮጲያውያንን በማጭበርበር በባዶ ቃላት በመደለል አገራችንን ኢትዮጲያን ለባለሀብቶች በመቸርቸር ህዝባችን አግኡን እንድያጣ በማደረግ ላይ ያላች ሁት :: ለጊዜው በመዋሸት የስልጣን እድሜህን ማረዘም ብትችልም ወድቀታችሁ የማይቀር ነው ::
_________________
United we stand, divided we fall!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
መቅደላዊ

ዋና ኮትኳች


Joined: 01 Dec 2009
Posts: 599
Location: Ethiopia

PostPosted: Sat Apr 10, 2010 10:41 am    Post subject: Reply with quote

ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው:
ሰላም ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ :-

ሣህሌ (ስዬ ) አብርሃ የተቻለውን ያህል ከለገሠ (መለስ ) የተሻለ ኦሪጅናል ወያኔ መሆኑን ለማሥመስከር ብቻ ሣይሆን በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተሻለ ሰው ሆኖ ለመታዬት እየጣረ ነው :: ስለ ወያኔና የሱዳን እስላማዊ አገዛዝ ይህንን ብሏል ::

Quote:
ኢህአዴግ ከሕዝብ በስተጀርባ የኢትዮ -ሱዳንን ድንበር ለማካለል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጥብቆ ይቃወማል፡፡

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሱዳን መልካም ግኑኝነት እንዲኖራት የመድረክ ፍላጎት እና እምነት ቢሆንም በኢትዮጵያ ሉኣላዊ መሬት ዋጋ እንዲሆን አይፈቅድም፡፡


ምንጭ :- አቡጊዳ : የባሕር በር አስፈላጊነትን አስምሮበት ከሱዳን ጋር በድብቅ የሚደረገዉን ስምምነት፣ የሶማሊያን ጦርነት መድረኩ አወገዘ

ቢያንስ አንድ ወያኔ ከሱዳን እስላማዊ አገዛዝ ጋር ኢትዮጵያን የሚጎዳ የሚሥጢር ድርድር እየተደረገ መሆኑን አምኗል ::

ተድላ


አቶ ስየ አብርሃ ወያኔ አይደሉም :: ለሱዳን ስለተሰጠው ትንተና ያቀረቡት እንደ አንድ ኢትዮጲያ ያለባቸውን የታሪክ አላፊነትን ለመወጣት ነው :: ሰለስጡን ትንትና አቶ ስየን ማመስገን ይገባናል :: ባንድ አገር የትሪክ ጉዙ ላይ አንድንድ ግልሰቦች የሚያሰልፎቸው ፈተናዎች አለኡ :: አቶ ስየም የወያኔ ደጋፊ ወይንም አባል ነበሩ :: ይሁንና ለአገራቸው ለኢትዮጲያ ለማገልገልና ግዳጃቸውን ለመውጣት ሲሉ በመደረክ የኢትዮጲያ ፖለቲካ ድርጅት ስር ሆነው ለምርጫ ቀርበዋል :; ህዝቡም መደርክን እንደሚመርጥ አንጠራጠርም :: አቶ ስየን መደግፍና ማበራታት አለብን ::
_________________
United we stand, divided we fall!
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ቢተወደድ

ዋና ውሃ አጠጪ


Joined: 21 Jul 2009
Posts: 1554
Location: Dabra Za`Yet

PostPosted: Sat Apr 10, 2010 12:28 pm    Post subject: Reply with quote

ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው:
ቢተወደድ እንደጻፈ(ች)ው:
ተላ እስቲ ባገራችን ምሁር የታጻፈ አምጣና አስነብበን :: እስከመቼ ድረስ ውድቀታችንን ለሚመኙ ባእዳን ነጋሪት ትጎሽማለህ ?

የኛው ችግር መፈታት አለበት በኛው ::


አንተ ወያኔ እንጂ ኢትዮጵያዊ አይደለህም :: ስለዚህ እኔ ኢትዮጵያዊው ካንተ ጋር እኩል ተቆጥሬ "እኛ " ብለህ ልትጠራኝ አትችልም ::

በገሃድ እና በኅሊና ያሠራችኋቸውን : ከፈቃዳቸው ውጪ ከአገራቸው እንዲሠደዱ ያደረጋችኋቸው አያሌ ኢትዮያውያን ምሁራን የሚሉትን ለማዳመጥ ጆሮውም : የሚጽፉትን ለማንበብና ለማገናዘብ ኅሊናው የላችሁም :: ስለዚህ ጌቶቻችሁ ፈረንጆች : ቻይኖች : ሕንዶች እና አረቦች የሚጽፉትን እያመጣን እናስነብባችኋለን ::

ተድላ


ይድረስ ለተላ ሀይሉ ኢትዮጵያዊነቴን ለመንጠቅ የተነሳ ብኩን ዜጋ ::

ኢትዮጵያዊነቴን ማንም አይሰጠኝም ማንም አይነጥቀኝም ::

ከጽሁፍህ መረዳት እንደምንችለው ጠባብነትህንና DICTATOR መሆንህን ያሳያል :: ለመሆኑ ፊደል ቆጥረሀል ?

ሌላው ያገራችን ምሁሮች የጻፉትን ለማገናዘብ ሕሊና የላችሁም ነው ያልከው ? ባንተ ሕሊና እንድንመራ አትጠብቅ :: አንተ አለህ አይደል በነጮች ሕሊና የምትመራ በግ :: እስከምቼስ የነሱ አለቅላቂ ሆነህ ትዘልቀዋልህ ? በርራስህ ስለማትተማመን ሁሌ አሉ : ተባለ : ዘገቡ እያልክ ታደርቀናለህ ::
_________________
When we do it right No-one remembers,
When we do it wrong No-one forgets.
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Send e-mail Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Sun Apr 11, 2010 4:32 am    Post subject: Reply with quote

ቢተወደድ እንደጻፈ(ች)ው:
ይድረስ ለተላ ሀይሉ ኢትዮጵያዊነቴን ለመንጠቅ የተነሳ ብኩን ዜጋ ::

ኢትዮጵያዊነቴን ማንም አይሰጠኝም ማንም አይነጥቀኝም ::


ወያኔነትን አምነህ ስትቀበል ኢትዮጵያዊነትን ክደኸዋል :: ስለዚህ እኔ ሣልሆን በራስህ ፈቃድ ኢትዮጵያዊነትን ትተህ ወያኔ ሆነሃል :: Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ቢተወደድ

ዋና ውሃ አጠጪ


Joined: 21 Jul 2009
Posts: 1554
Location: Dabra Za`Yet

PostPosted: Mon Apr 12, 2010 1:38 am    Post subject: Reply with quote

ነገሮች ሁሉ ሳይምታቱብህ የቀረህ አትመስልም ::

ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው:
ቢተወደድ እንደጻፈ(ች)ው:
ይድረስ ለተላ ሀይሉ ኢትዮጵያዊነቴን ለመንጠቅ የተነሳ ብኩን ዜጋ ::

ኢትዮጵያዊነቴን ማንም አይሰጠኝም ማንም አይነጥቀኝም ::


ወያኔነትን አምነህ ስትቀበል ኢትዮጵያዊነትን ክደኸዋል :: ስለዚህ እኔ ሣልሆን በራስህ ፈቃድ ኢትዮጵያዊነትን ትተህ ወያኔ ሆነሃል :: Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool Cool

ተድላ

_________________
When we do it right No-one remembers,
When we do it wrong No-one forgets.
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Send e-mail Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Sat Apr 24, 2010 6:12 am    Post subject: Reply with quote

ሰላም ውድ ወገኖቼ :-

በአሜሪካን አገር የሕዝብ ዜና ማሠራጫ ተቋም (Public Broadcasting Corporation - PBS) በሚያቀርባቸው ጥናታዊ የቴሌቪዝን እና የሬድዮ መርሃ -ግብሮቹ ተዓማኒነቱ ከፍተኛ የሆነና የታወቀ ነው :: ሠሞኑን ወያኔ በጠራራ ፀሐይ ስለሚቸበችበው የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት - መሬት አንድ ጥናታዊ ዘገባ አቅርቧል :: ዘገባውን ያዘጋጀው ጄፍሬይ ብራውን ሲሆን ፊልሙን ያቀናበረው ደግሞ ፍሬድ -ሣም ላዛሮ ይባላል ::

ከአምሥት ሚሊዮን የማያንሱ ኢትዮጵያውያን በዕለት -ተዕለት የምግብ ዕርዳታ በሚኖሩበት አገር መሬት ተርፎ ለውጪ የዘመኑ ቅኝ ገዢዎች 99 ዓመታት በሊዝ ይሸጣል :: ይገርማል የወያኔ ነገር Rolling Eyes Rolling Eyes Rolling Eyes ይህ ቀን የማያልፍ መስሏቸው ምናለ ለልጆቻቸው የሥደት ሥፍራ እንኳን ባያሣጧቸው ?

ፊልሙ 8 ደቂቃዎች እርዝማኔ ያለው ነው : ተከታተሉት ::

Public Broadcasting Service
April 22, 2010 . Ethiopias abundant farming investments leave many still hungry


ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Sun May 30, 2010 3:49 am    Post subject: Reply with quote

ሰላም ውድ ወገኖቼ :-

ወያኔዎች የኢትዮጵያን መሬት ለአረቦች ሲቸረችሩ እግረ -መንገዳቸውን ለወደፊቱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጠላቶችን ለመትከል እንደሆነ ሣይታለም የተፈታ ሃቅ ነው :: የሳዑዲ ዲታዎች በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠሩት ሌላ አገር የሚያርሱት መሬት አጥተው አይደለም - ሌላ አፍጋኒስታን በአፍሪቃ ቀንድ ለመትከል ካላቸው የረዥም ጊዜ ዕቅድ አኳያ እንጂ ::

እስኪ ይህንን 'Arab News' ላይ የወጣ ዜና አንብቡት ::

ምንጭ :- K.S. RAMKUMAR, ARAB NEWS, Published: May 29, 2010 23:16 Updated: May 29, 2010 23:16. Saudis invest heavily in Ethiopian farm sector

Quote:
Saudis invest heavily in Ethiopian farm sector

JEDDAH: Saudi trade and investment in Ethiopia is expanding. The investment increase is particularly seen in the agricultural sector and is in line with Custodian of the Two Holy Mosques King Abdullahs initiative to provide food security for the Kingdom. Agricultural lands being leased by Saudis have been increasing by the day in Ethiopia, Ethiopian Consul General Tekleab Kebede told the community at the countrys national day celebrations at the consulate over the weekend.

Kebede said many Saudis and local companies had been signing contracts with landowners across Ethiopia to produce grains and other agricultural products. Rice produced by a prominent Saudi company was presented to the king recently, he said.

Saudis are allowed 100 percent investment in projects in Ethiopia. They either lease plots of land or enter into deals in cooperation with local partners, the consul general said. Such investments are now worth millions of dollars, he added.

We have plenty of land, water and abundant labor, while Saudis have capital. We have been giving the message to Saudis that we complement each other in boosting our bilateral business, investment and trade volumes. After all, both countries have close geographical proximity, Kebede said.

Kebede said the bilateral trade volume had exceeded $500 million, with the balance remaining in favor of the Kingdom due to heavy oil imports into his country. The Kingdom remains our second trading partner, with our trade continuing to increase, he said, adding that Saudi investors were prominent in his country and have been increasingly investing in agriculture, tourism, hotels, mining and manufacturing.

The consul general said a ministerial delegation belonging to agriculture and rural development had a successful visit to the Kingdom earlier in May. They discussed with their Saudi counterparts in Riyadh and Jeddah new proposals related to livestock and meat exports to the Kingdom, he said. We have huge livestock potential. We have already been exporting livestock and meat, but our new thrust is in further strengthening our presence in the Kingdoms food sector, Kebede added.

The consul general said May 28, 1991 marked the end of 17 years of war, thus heralding peace and stability that resulted in the countrys march toward economic, social and political progress.

Ethiopia is changing for the better, and the country is open for business and foreign investment, he said and urged Saudis to take advantage of the congenial investment atmosphere.

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Wed Jun 09, 2010 4:24 pm    Post subject: Reply with quote

ሰላም ውድ ወገኖቼ :-

ወያኔ የኢትዮጵያን መሬት ለህንዶች : አረቦች : ቻይኖች : ወዘተርፈ መቸርቸሩን ቀጥሏል :: ኢትዮጵያውያን የሌላቸውን የመሬት ባለቤትነት መብት የወያኔ ወዳጅ የሆኑ የዓለም -አቀፉ ማፊያ ጓዶቹ በፈለጉት መሬት መጠን ያገኛሉ :: ይህም ለልማት ነው ተብሎ ይደሰኮርልናል :: የሚገርመው ግን ይህ ሁሉ መሬት እየተቸበቸበ የወያኔ ወዳጆች 'ከሚያለሙት መሬት ' የሚመረተው ምርት ለአገር ውስጥ ፍጆታ ሣይሆን ወደማፊያዎቹ አገሮች የሚላክ ነው :: ኢትዮጵያውያን ግን እህል እንደሚያበራይ ከብት አፋቸው ተሸብቦ ከአሜሪካ እና ካናዳ የሚላክ 'ዘረ -ልውጥ ' የስንዴ ዕርዳታ ይለመንባቸዋል :: ድንቄም ልማት Razz Razz Razz

በውድነህ ዘነበ : ሪፖርተር ጋዜጣ : ረቡዕ ሰኔ 2 ቀን 2002 .. :: የሕንድ ኩባንያ 10 ሺሕ ሔክታር መሬት ተረከበ

Quote:
የሕንድ ኩባንያ 10 ሺሕ ሔክታር መሬት ተረከበ

(በውድነህ ዘነበ )

የፌዴራል መንግሥት ከክልሎች የተረከበውን ሠፋፊ መሬት እንዲያስተዳድር የወከለው የገጠር እና ግብርና ልማት ሚኒስቴር፣ በዓለም ላይ ከአኩሪ አተር ምግብ በማምረት ለሚታወቀው የሕንዱ ሩቺ ሶያ ኢንዱስትሪስ ሊሚትድ 10"000 ሔክታር መሬት ሰጠ፡፡ ኩባንያው 100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጭ በማድረግ ዘመናዊ የአኩሪ አተር እርሻ ለማቋቋም አቅዷል፡፡
የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ይህንን መሬት የሰጠው በጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ሲሆን፣ በክልሉ ሠፋፊ የእርሻ መሬት ከተረከቡት ግዙፍ ኩባንያዎች ሦስተኛው ሆኗል፡፡

በክልሉ በመጀመርያ ቦታ የተረከበው ካናቱር አግሮ ፕሮዳክት ኩባንያ በክልሉ 300"000 ሔክታር መሬት የተረከበ ሲሆን፣ በዚህ መሬት ላይ የፓልም ዘይት፣ ሩዝ እና ስኳር ያመርታል፡፡

ሌላኛው ኩባንያ በሼሕ መሐመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ የተመሠረተው ሳውዲ ስታር ግብርና ልማት ኩባንያ ሲሆን፣ ይህ ኩባንያ በክልሉ 10"000 ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡

ኩባንያው በዚህ መሬት ላይ ሩዝ የማልማት ዕቅድ ያለው ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት ሁለቱም ኩባንያዎች ሥራው ውስጥ ገብተዋል፡፡

በክልሉ የሦስተኛ ዘመናዊ እርሻ ባለቤት የሆነው ሩቺ፣ በዚህ መሬት ላይ አኩሪ አተር የሚያለማ ሲሆን፣ በቀጣይነት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሚረከበው መሬት ላይ ደግሞ ምርቱን ወደ ተለያዩ የምግብ ዓይነቶች የሚቀይርበትን ፋብሪካ የመገንባት ዕቅድ ይዟል፡፡

"በሚቀጥለው ጥቅምት ወር ላይ ምርት ለመጀመር ኩባንያው ሙሉ ዝግጀት አድርጓል " ሲሉ በሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት ድጋፍ ሰጪ ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ከበደ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

"ይህንን ፕሮጀክት በጥሩ ሁኔታ ካካሔደ የፓልም ዛፍ ለማምረት የጠየቀውን ቦታ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እንሰጠዋለን፤ " ሲሉ አቶ ኢሳያስ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከተመሠተ 25 ዓመታትን ያስቆጠረው ሩቺ በዓመት 4 ሚሊዮን ቶን አኩሪ አተር የማቀነባበር አቅም ያለው ሲሆን፣ ተረፈ ምርቱም ለከብቶች መኖ ይውላል፡፡

ኩባንያው ይህንን ምርቱን ጃፓን፣ ኢንዶኔዥያ፣ ታይላንድ፣ ቬትናም፣ ደቡብ ኮሪያ እንዲሁም ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ይልካል፡፡

የፌዴራል መንግሥት በውክልና ከክልሎች ተረክቦ ለሠፊፋ የግብርና ልማቶች መሬት ማቅረብ ከጀመረ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወራት በላይ ሆኗል፡፡

የተረከባቸው ቦታዎች የሚገኙት ከአዲስ አበባ፣ ከድሬዳዋና ከሐረር በስተቀር በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ሲሆን፣ በተለይ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ጉምዝና ደቡብ ክልል ኢንቨስተሮቹን ስበዋል፡፡

በተለይ ጋምቤላና ቤንሻንጉል ጉምዝ የሩዝ እና ከዕፅዋት የሚገኝ ነዳጅ አምራቾችን ፍላጐት ሲስቡ፣ ደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ አካባቢ የጥጥ ኢንቨስትሮችን ትኩረት እየሳበ ነው፡፡

ለባለሀብቶቹ ቦታ የሚያቀርበው የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር በየወሩ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሪፖርት የሚያቀርብ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩም በቅርብ ከሚከታለሏቸው ዘርፎች አንዱ ነው፡፡

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
ተድላ ሀይሉ

ዋና አለቃ


Joined: 17 Mar 2006
Posts: 4459
Location: ኢትዮጵያ

PostPosted: Mon Jun 21, 2010 10:16 pm    Post subject: Reply with quote

ሰላም ውድ ወገኖቼ :-

ወያኔ ምን ያልቸበቸበው የኢትዮጵያ አንጡራ ሀብት አለ ? ሕዝቧንስ በባርነት ወደ አረብ አገሮች መሸጡን እንደ ትልቅ ተግባር ቆጥሮት በኤምባሲዎቹ አማካይነት ያስተጋባው የለም ?

1997 .. የምርጫ ድራማ በኋላ ወያኔ በከተሞች የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ በተለያዩ የቅጣት መንገዶች ያሠቃያል :: በተለይ መጠለያ መንፈግ እና ቤት ያላቸውንም ቤታቸውን አፍርሶ ሜዳ ላይ መጣል የተለመደ የወያኔ ተግባር ነው :: ይህም አልበቃው ብሎ የከተማውን ምርጥ ምርጥ መሬት ለባለሟሎቹ እና የውጪ አጋሮቹ 'ኢንቨስትመንት ' ሥም በጣም በርካሽ ዋጋ ይቸበችባል :: በተቃራኒው ከአያት ቅድመ -አያት ጀምሮ ርስታቸው ከሆነው ሥፍራ ዜጎች እየተፈናቀሉ ተጨማሪ ገንዘብ ከፍለው ከከተማው ዳር ይጣላሉ :: 'ኢትዮጵያ ዛሬ ' የሰኔ 14 ቀን 2002 .. ዘገባ ይህንን ያመለክታል ::

Quote:
ከሁለት ሺህ በላይ ተፈናቃይ ነዋሪዎች ሃያ እና አስር ሺህ ብር ተጠየቁ

Monday, 21 June 2010 07:18

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2002 .. June 21, 2010) በአዲስ አበባ ከአራት ኪሎ ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ያሉ ቤቶች እንዲፈርሱ ተወስኖ፤ መሬቱ ለግል ባለሀብቶች መሸጡ ታወቀ። ተፈናቃዮቹ ከአቅማቸው በላይ ገንዘብ ከፍለው ኮንደሚንየም ቤቶች ውስጥ እንዲገቡ ተጠየቁ።

መንግሥት መሬቱን ሲሸጥ በአካባቢው በቀበሌም ይሁን በኪቤአድ ቤት ተከራይተው ይኖሩ ለነበሩ ሰዎች ተለዋጭ ቤት የመሥጠት ግዴታ አለበት። ይሁን እንጂ ”ፉሪ” የተባለ አካባቢ መንግሥት ወዳስገነባው ኮንደሚንየም ቤቶች የሚፈናቀሉት ነዋሪዎች እንዲገቡ ተነግሯቸዋል። ለዚህም ተፈናቃዮቹ ቅድሚያ ክፍያ 20 ሺህ ብር ተጠይቀዋል።

ባለሁለት መኝታ ቤት ኮንደሚንየም ውስጥ ለሚገባ ሃያ ሺህ ብር፣ ባለአንድ መኝታ ቤት ውስጥ ለሚገባ ደግሞ አስር ሺህ ብር ቅድሚያ ክፍያ እንዲከፍሉ ተነግሯቸዋል። በዚህም ምክንያት በርካቶቹ የአካባቢው ነዋሪዎች የተጠየቁትን ክፍያ የመክፈል አቅም ስለሌላቸው ከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ መሆናቸውን ለመረዳት ችለናል።

የተጠየቁትን ገንዘብ ፈፅሞ ማግኘትም ሆነ መክፈል አንችልም ያሉ ወገኖች ደግሞ፤ በከተማይቱ በሚገኙ አንዳንድ መንግሥታዊ መጋዘኖች ውስጥ መቀመጥ እንደሚችሉ ተገልፆላቸዋል።

ይህ የመንግሥት ውሳኔ ተግባራዊ የሚሆነው ከሰኔ 30 ቀን እስከ ሐምሌ 15 ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ይህን መሰል እርምጃ ሲወሰድ ቢያንስ የአንድ ዓመት የዝግጅት ጊዜ መሰጠት ነበረበት ሲሉ እርምጃው ተገቢና -ሰብዓዊነት የጎደው ነው በማለት ድርጊቱን ኮንነዋል።


ምንጭ :- ኢትዮጵያ ዛሬ ::

ተድላ
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
Back to top
View user's profile Send private message Report post
Display posts from previous:   
Post new topic   Reply to topic    WARKA Forum Index -> Warka Politics - ዋርካ ፖለቲካ All times are GMT + 1 Hour
Goto page Previous  1, 2, 3, 4 ... 13, 14, 15  Next
Page 3 of 15

 
Jump to:  
You cannot post new topics in this forum
You cannot reply to topics in this forum
You cannot edit your posts in this forum
You cannot delete your posts in this forum
You cannot vote in polls in this forum


Provided by CyberEthiopia.com , powered by phpBB © 2001, 2005 phpBB Group , Original Amharic translation by Ethiopic Open Source Translation modified by CyberEthiopia