|
|
|
| View previous topic :: View next topic |
| Author |
Message |
ዞብል 2

Joined: 30 Jan 2004 Posts: 1606
|
Posted: Wed Dec 16, 2009 2:49 am Post subject: |
|
|
ስማ 3ኛ ጥያቄህ ብርቱኳን ኢትዮጵያን ታውቃለች ወይ ላልከው
ኢትዮጵያ የብርቱኳን ሚደቅሳ የአያት ቅድመ አያት የአባት እናቷ ሀገር የተወለደችበትና እትብቷ የተቀበረበት
ከአንደኛ ደረጃ እሰከ ዩንቨርሲቲ ትምህርት ተምራ ለሰራ የበቃችበት
ለህግና ለሰብዓዊ መብት መከበር ስትል ወህኒ የወረደበችበት ሀገሯ ነት
ስማ አሻውይና (ጋሽ ወያኔ ) አንተ የትግራይ ነፃአውጪ ብለህ ከበሮና ክላሽ ተሸክመህ ጫካ የገባህ ቅጫማም ሰውን ኢትዮጵያን ታውቃላችሁ ብለህ ስትጠይቅ ትንሽ አታፍርም
ወይናና አንተ እራስህን የትግራይ ነፃአውጪ ብለህ ደደቢት በርሀ ቢጫ ወባ ሲያባርርህ የነበርከውን ኢትዮጵያን አውቃታለሁ ወይ ብለህ ጠይቅ የሆንክ ግሽጣ ራስ ወያኔ
ዞብል ከፒያሳ |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ዞብል 2

Joined: 30 Jan 2004 Posts: 1606
|
Posted: Wed Dec 16, 2009 5:30 pm Post subject: |
|
|
አሻወይና የስራ ልምድ
የወያኔ የሥራ ልምድ መስፍርት ማለትም
1=ሀገር መካድ
2=የውሸት ታሪክ መተረክ
3=በፈንጂ መንገድና ድልድይ ማፈንዳት
4=የርሀብተኛ እህል መዝረፍ
5=የማያውቁትን አውቃለሁ ብሎ ሀገርና ወገንን አደጋ ላይ መጣል
**እነዚህ ናቸው የወያኔ የስራ ልምድ መመዘኛዎች ስለሆነም ወ /ት ብርቱኳን ሚደቅሳ አንዱንም አታሟላም
ዞብል ከፒያሳ |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ኣሸወይና

Joined: 12 Sep 2009 Posts: 70
|
Posted: Wed Dec 16, 2009 9:39 pm Post subject: |
|
|
| ዞብል 2 እንደጻፈ(ች)ው: | ስማ 3ኛ ጥያቄህ ብርቱኳን ኢትዮጵያን ታውቃለች ወይ ላልከው
ኢትዮጵያ የብርቱኳን ሚደቅሳ የአያት ቅድመ አያት የአባት እናቷ ሀገር የተወለደችበትና እትብቷ የተቀበረበት
ከአንደኛ ደረጃ እሰከ ዩንቨርሲቲ ትምህርት ተምራ ለሰራ የበቃችበት
ለህግና ለሰብዓዊ መብት መከበር ስትል ወህኒ የወረደበችበት ሀገሯ ነት
ስማ አሻውይና (ጋሽ ወያኔ ) አንተ የትግራይ ነፃአውጪ ብለህ ከበሮና ክላሽ ተሸክመህ ጫካ የገባህ ቅጫማም ሰውን ኢትዮጵያን ታውቃላችሁ ብለህ ስትጠይቅ ትንሽ አታፍርም
ወይናና አንተ እራስህን የትግራይ ነፃአውጪ ብለህ ደደቢት በርሀ ቢጫ ወባ ሲያባርርህ የነበርከውን ኢትዮጵያን አውቃታለሁ ወይ ብለህ ጠይቅ የሆንክ ግሽጣ ራስ ወያኔ
ዞብል ከፒያሳ | አየህ የናንተ የፖለቲካ ብስለት ስድብ ብቻ ነዉ !!የሄንንም እነ ፍሮይድ ምን ይሉታል መሰልህ Defensive Mechanism ይባላል !አየህ የማትረዳዉ ነገር አንተን መሰሎችም ጭምር ዕኔ የወያኔ ደጋፊ አይደልሁኝም !! ነገር ግን ወያኔ ስለሆኑ ሳይሆን እንዳንተ በደመ ነፍስ የምጠላቸዉ ወይንም የምወዳቸዉ በዲያሎግ ብቻ ነዉ ልግባባም ላልግባባም የምችለዉ !!ዕንዳንተ አይነቱ ስለዲሞክራሲ ዕና ነጻ አስተሳሰብ ወይንም አመለካከት ያለዉ ህብረተሰብ ጋራ እየኖርን እንዼት የደማንለት ዲሞክራሲን ልናገኛት እንደምንችል አይገባኝም !! |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ዞብል 2

Joined: 30 Jan 2004 Posts: 1606
|
Posted: Thu Dec 17, 2009 1:51 am Post subject: |
|
|
ስማ ወይናና ስድብ ነው ያልከው ያንተ አይብስም የተወለደችበትን አገር አታውቅም ስትል የማንን አገር እንድታውቅልህ ትፈልጋለህ
ወያኔነትህ ከፅሁፍ ያስታውቃል ያውም ሹሉ ጭንቅላትህ የሚያብረቀርቅ ከላባ ካድሬ
አንተ የደማህለትና የቆሰልክለት ዲሞክራሲ በጠመንጃ አፈሙዝ ህዝብን አፍኖ ማኖር ነው
ስማ ያንተ የወያኔ አለቆች ከየትኛው ኮሌጅ በፖለቲካል ሳይንስ ተመርቀው ነው የሀገር መሪ የሆኑት የስራ ልምድስ የት ነው ያገኙት
መልሱ ናቅፋና ደደቢት በርሃ
ባለ ቅኔው ድንቁርና ያስፈራኛል ብለዋል አሁንም ከአንተ አይነቱ ድንቆሮ ማይም እግዜር ይጠብቀን
ዞብል ከፒያሳ |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ብርቄነህ

Joined: 22 Jan 2009 Posts: 306
|
Posted: Thu Dec 17, 2009 3:08 am Post subject: |
|
|
| ዞብል 2 እንደጻፈ(ች)ው: | ስማ ወይናና ስድብ ነው ያልከው ያንተ አይብስም የተወለደችበትን አገር አታውቅም ስትል የማንን አገር እንድታውቅልህ ትፈልጋለህ
ወያኔነትህ ከፅሁፍ ያስታውቃል ያውም ሹሉ ጭንቅላትህ የሚያብረቀርቅ ከላባ ካድሬ
አንተ የደማህለትና የቆሰልክለት ዲሞክራሲ በጠመንጃ አፈሙዝ ህዝብን አፍኖ ማኖር ነው
ስማ ያንተ የወያኔ አለቆች ከየትኛው ኮሌጅ በፖለቲካል ሳይንስ ተመርቀው ነው የሀገር መሪ የሆኑት የስራ ልምድስ የት ነው ያገኙት
መልሱ ናቅፋና ደደቢት በርሃ
ባለ ቅኔው ድንቁርና ያስፈራኛል ብለዋል አሁንም ከአንተ አይነቱ ድንቆሮ ማይም እግዜር ይጠብቀን
ዞብል ከፒያሳ |
| Quote: | ባለ ቅኔው ድንቁርና ያስፈራኛል ብለዋል አሁንም ከአንተ አይነቱ ድንቆሮ ማይም እግዜር ይጠብቀን
|
ዞብልዬ ! ጥሩ መደምደሚያ ነው ያስቀመጥከው : ከእንደዚህ አይነቱ ጋር ውለህ የምታገኘው ትርፍ ሳይሆን ኪሳራ ብቻ ስለሚሆን እንዳልከው ይሰውረን ማለት ነው የሚሻለው ! |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ኣሸወይና

Joined: 12 Sep 2009 Posts: 70
|
Posted: Fri Dec 18, 2009 9:45 pm Post subject: |
|
|
| ዞብል 2 እንደጻፈ(ች)ው: | ስማ ወይናና ስድብ ነው ያልከው ያንተ አይብስም የተወለደችበትን አገር አታውቅም ስትል የማንን አገር እንድታውቅልህ ትፈልጋለህ
ወያኔነትህ ከፅሁፍ ያስታውቃል ያውም ሹሉ ጭንቅላትህ የሚያብረቀርቅ ከላባ ካድሬ
አንተ የደማህለትና የቆሰልክለት ዲሞክራሲ በጠመንጃ አፈሙዝ ህዝብን አፍኖ ማኖር ነው
ስማ ያንተ የወያኔ አለቆች ከየትኛው ኮሌጅ በፖለቲካል ሳይንስ ተመርቀው ነው የሀገር መሪ የሆኑት የስራ ልምድስ የት ነው ያገኙት
መልሱ ናቅፋና ደደቢት በርሃ
ባለ ቅኔው ድንቁርና ያስፈራኛል ብለዋል አሁንም ከአንተ አይነቱ ድንቆሮ ማይም እግዜር ይጠብቀን
ዞብል ከፒያሳ | ዕራስክህን ተመልከት !አንድ ዕጣጥክን ወደሰዎች ከመጠቆምህ በፊት አራት ጣቶችህ አንተኑ እንደሚጠቁሙ ብታዉቅ ምን ያክል ትበስል ነበር !!
ከሰድብ በስተቀር አንተም ሆንክ ብርቄነህ ምንም አይነት የፖለቲካ clue የላችሁም !!ታዲያ ከንደ ዕናንተ አይነቱ የነብርቱካን hard core fans ጋር ምን መነጋገር ይቻላል !!ዕዚህ ላይ አንድ በርግጠኝነት መናገር የምፈልገዉ ዕኔ ከላይ ዕንዳስቀመጥኩት የማንም ፖለቲካል ግሩፕ ወይንም ፓርቲ አባልም ደጋፊም አይደለሁኝም ""ነገር ግን ገና ለገና ወያኔ ጋራ የማልግባባበት አንዳንድ ነጥቦች ቢኖሩኝም 100%ግን ጥሩ ሲሰሩ አይኔ እያየ መጥፎ ሰሩ ብዬ እንደዕናንተ ነጩን ጥቁር ብዬ መከራከር አልወድም !!ይሄ እንግዲህ ወያኔ ካስባለኝ gohead
አሁንም ወደድክም ጠላህም ብርቱካንም ሆነ ሌሎች የቅንጅት የአመራር አካላት ኢትዮጲያን አያዉቁኣትም ;;ለአንተ ኢትዮጲያ ማለት አዲስ አበባ ዉስጥ ማደግ ከሆነ በርግጥ ልክ ብለሀል ኢትዮጲያን በዛ መልኩ ታዉቃታለህ ;;ለኔ ግን ኢትዮጲያ ማለት የኢትዮጲያ ሰፊ ህዝብ ገበሬዉን ይመልከታል !!ዕነ ብርቱኣ ግን የትኛዉን ገበሬ አዉቅዉት ይሆን ?እንዲህ በስራት መንገላታቸዉ ?ቅቅቅቅቅቅቅቅቅ ወይንስ የነርሱ እንግልት እንደፖሊሱ ዘገባ ይቅርታ አልጠየኩም ይሆን እዉነቱ ?ቅቅቅቅቅቅቅ ይህንን ብቻ ካንተ እንድማር እወዳለሁኝ ? |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ዞብል 2

Joined: 30 Jan 2004 Posts: 1606
|
Posted: Fri Dec 18, 2009 11:27 pm Post subject: |
|
|
ስማ ተጋዳላይ ወይናና መጀመሪያ አስተካክለህ ፃፍ ፊደሎቹን ብቴስታ አታላጋቸው
የራስህ ፅሁፍ ለራስህ መልስ ስለሚሰጥህ ፅሁፍህን መልሰህ አንበው
የገጠርና የከተማ ኢትዮጵያ የሚለውን ክፍፍልህን እዛው ከወያኔ ጓዶችህ ጋር ሆነህ አላዝን የውቅሮ ጆሊ
ይህ መድረክ ለአንተ ስለማይመጥን ሰላም ስጠን
ዞብል ከፒያሳ |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ብርቄነህ

Joined: 22 Jan 2009 Posts: 306
|
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ብርቄነህ

Joined: 22 Jan 2009 Posts: 306
|
Posted: Tue Dec 22, 2009 5:42 pm Post subject: |
|
|
ሰላም አባዊርቱ :
መቼም እስካሁን ድረስ :በዚህ ርዕስ ላይ ተፈጥሮ የነበረው ውዥንብር ከማንኛው ወገን እንደተቀስቀሰ ትረዳለህ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ :: ያንተናንና የመሰሎችህን መተባበር አጥብቀው የሚጠሉ ወገኖች : መንገዳቸው ብዙ ነው :: ይሁንና ቆም ብለን ማሰብ ከቻልን ማን ምን ለማድረግ እንደሚፈልግ መረዳት ሊያቅተን አይችልም ::ምክንያቱም ሁላችንም የአንድ ወንዝ ልጆች ነንና :: በተጨማሪም እግዚአብሄር ለነርሱ የተለየ የማሰቢያ አካል እንዳልፈጠረላቸውም እርግጠኞች ነንና ::
ስለዚህ ከእስካሁኑ ቆይታህ ትክክለኛውን ሁኔታ ተረድተህ ወደዚህ ትመለሳለህ የሚል ጽኑ እምነት ነው ያለኝ ::
ሰላም ሁን ወንድሜ !
| ብርቄነህ እንደጻፈ(ች)ው: | | አባዊርቱ እንደጻፈ(ች)ው: | እረ ዋናው ጉዳይ ተረሳ እዚህ !
እስቲ ለምን ብርቱካንን እንደምታደንቁ እዚህ ጻፍ ጻፍ አርጉ !
እኔ በቀጥተኛነቱዋና ከምንም ንክኪ እንደሌላት ስለማምን ነው ...በሰፊው ተመልሼም እመጣበታለሁ ! |
ሰላም አባዊርቱ .
እንኳን ወደገንባሄው ቤትህ ተመለስክልን ::
ዋናው ጉዳይ ተረሳ ? ላልከው መልሴ በፍጹም አይረሳም ነው ::
ብርቱካን ትቅደም ያልኩበትም ዋነኛው ምክንያት ብርቱካን እንዳትረሳ በማሰብ ነው :: ትርፍ ሰአትና ምቹ ቦታ ጠብቀን ሳይሆን በማንኛውም ሰአትና ቦታ ብርቱካንን ለማስፈታት የኢትዮጵያ ህዝብ መታገል ያለበት መሆኑን ለመጠቆም ስል ነው ይህንን ርእስ የከፈትኩት ::
በተረፈ ስለብርቱካን ያለህ አመለካከት እዚህ አምድ ላይ እየገቡ ተቃውሞ ከሚያቀርቡት ግለሰቦች አመለካከት በፍጹም የተለየ በመሆኑ ስለአንተ አመለካከት ያለኝ አክብሮቴ እንደተጠበቀ ነው ::
ወያኔ በአገዛዝ ዘመኑ ውስጥ ከነደፋቸው የስራ እቅዶች መካከል 100% ግቡን የመታለት እቅድ ቢኖር : በሰዎች መካከል አለመተማመንን የመፍጠርና የአንድነት ስሜትን የማስወገድ እቅዱ እንደሆነ የሚጠራጠር ይኖራል ብዬ አልገምትም ::ይህም በዚህች በትንሿ የውይይት ርዕስ ላይ እንኳ ሳይቀር ሲንጸባረቅ ለማየት ተችሏል ::
በተረፈ ስለ ብርትካን ላቀረብከው ጥያቄ ትንሽ ጊዜ ሳገኝ የአቅሜን ያህል ለመጠቆም እመለሳለሁ ::
እስከዚያው ሰላም ሁን ! |
|
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ደሊል

Joined: 22 Dec 2003 Posts: 44
|
Posted: Tue Dec 22, 2009 10:02 pm Post subject: ብርትኳንና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ |
|
|
ታህሳስ 12 ቀን 2002 ዓ .ም
በዚምባብዌና በኬንያ እንደታየዉ የጥምር መንግስት መመሥረት የሚቻልበት ሁኔታ ሊኖር ይችል እንደሆን በቅርቡ ከጋዜጠኖች ተጠይቀዉ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ሲመልሱ፣ የቀለም አብዮት በኢትዮጵያ እንደማይሰራ በማስረዳት ከምርጫ በኋላ የሚነሳ ማናቸዉም አይነት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ የትም እንደማያደርስና መዘዙ የከፋ እንደሚሆን ለማስጠንቀቅ ሞክረዋል። አንዳንድ የተቃዋሚ መሪዎች፣ አሁንም ካለፈዉ ስህተት እየተማሩ እንዳልሆነና አሁንም ምርጫዉን በመጠቀም አመጽ ለመቀሰቀስ ሃሳብ ሊኖራቸው እንደሚችሉም ያላቸዉን ግምት ሰጥተዋል።
እንደምሳሌም የጠቀሱት ለአንድ አመት ያህል በግፍና በጭካኔ ታስራ በቃሊቲ እሥር ቤት እየተንገላታች ያለችዋን ታላቅ የሕዝብ መሪ ክብርት ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳን ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለአገር ዉስጥ ጋዜጠኖች በወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ዙሪያ የተናገሩት የሚከተለዉን ነበር፡
«ወ /ት ብርቱካንን በምሳሌለነት ብንወስድ ምህረት አልጠየቅንም ብለዉ፣ ሽማግሌ ቢላክ አምባሳደር ቢላክ አልሰማም አልቀይርም፣ በዉጭ ሄጄ የተናገርኩትን አልክድም፣ አልቀየርም ብለዉ ያሉት። ደጋፊዎቻቸዉ በሚፈጠሩት ብጥብጥ ወይም በዉጭ ኃይሎች ጫና በአጭር ጊዜ ዉስጥ ከእሥር ቤት እወጣለሁ የሚል ጠንካራ አቋም ስለነበራቸዉ ነው። በወቅቱ ግን በተደጋጋሚ ተነግሯቸዋል። ስህተት እንደሆነ። ከገቡ እንደማይወጡ። ስለዚህ ዋናዉ ነገር ሳይገቡ ቢቀሩ ለሁላችንም እንደሚበጅ በተደጋጋሚ ተነግሯቸዋል። ለአንድ ወር ያህል መንግስት ለምኗቸዋል። በቀጥታም በተዘዋዋሪ መንገድም። ለምን ቢባል ማን ነዉ የሚጠቀመዉ ከዚህ። መንግስት የሚያገኘው አምስት ሳንቲም ጥቅም የለዉም።»
ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳን ለማስፈታት የተቋቋመዉ ግብረ ኃይል፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ላይ ያቀረቡት ክስ አሳዝኝ፣ ዉሸት የተሞላበትና ይናጋሩበት ከነበረዉ ሃሳብ ጋር የማይገናኝ እንደሆነ ለማሳወቅ እንወዳለን።
በመጀመሪያ ደረጃ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ሕገ መንግስቱን አክብራ፣ በሕጋዊ መንገድ ከትግል አጋሮቿ ጋር አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን መሥርታ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የተንቀሳቀሰች የአንድ ትልቅ የፖለቲካ ፓርቲ ሊቀመንበር ናት። የ“ቀለም አብዮት“ ለማካሄድም ሆነ ማናቸዉም የባለሥልጣናትን ፍቃድ ያላገኘ ሰላማዊ ሰልፎችም ሆነ ስብሰባዎች ለማድረግ የተንቀሳቀሰችበት ጊዜ የለም። «ፍየል ወዲህ ቅምዝም ወዲያ» እንደሚባለዉ እኝህ ታላቅ የሰላምና የፍትህ ታጋይን ጠቅላይ ሚኒስትሩ «አመጽ እንደቀሰቀሱ» ወይንም «አመጽ ለመቀስቀስ እንዳሰቡ» አድርገዉ በማይገናኝ መልኩ ከ“ቀለም አብዮት“ አራማጆች ጋራ ማገናኘታቸዉ ለምን እንደሆነ ሊገባን አልቻለም።
ሽምግሌዎችና አምባሳደሮች አማላጅ እንደላኩ በመግለጽ አቶ መለስ ዜናዊ፣ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ «በዉጭ የተናገርኩትን አልቀይርም። ምህረት አልጠየኩም» ብለዋል ሲሉ እርሳቸዉና መንግስታቸዉ «አዛኝ» ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ግን »ግትር» እንደሆኑ ለማሳየት ሲሞክሩም ታዝበናል።
ጠቅላይ ሚኒሰትር መለስ ዜናዊ በዚህ ቃለ መጠይቅ ወቅት እንደ አዲስ ነገር፣ አዲስ ዘመንን የመሳሰሉ አገር ቤት የሚታተሙ ጋዜጦችን እንደማያነቡና በፈረንጆች የሚታተመው ዘኢኮኖሚስት የሚባለዉ ማጋዚን ግን እንደማያመልጣቸዉ ገልጸዋል።
ምናልባትም አዲስ ነገርን ወይንም አዲስ አድማስን የማንበብ ልማድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢኖራቸዉ ኖሮና ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ወደ እሥር ቤት ከመወሰዷ አንድ ቀን በፊት «ቃሌ» በተሰኘዉ ጽሁፏ የጻፉችዉን ቢያነቡ ኖሮ ከላይ የተጠቀሰዉን ፍጹም የተሳሳቱ አባባሎች በአደባባይ ላይናገሩ ይችሉ ነበር።
Last edited by ደሊል on Tue Dec 22, 2009 10:08 pm; edited 2 times in total |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ደሊል

Joined: 22 Dec 2003 Posts: 44
|
Posted: Tue Dec 22, 2009 10:05 pm Post subject: |
|
|
ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ቃሌ በተሰኘዉ ጽሁፏ ፡
«በሽማግሌዎች የእርቅ ማግባቢያ መንፈስ መሰረት በፖለቲካ የተቀሰቀሰዉን ክስ ፖለቲካዊ እልባት ለመስጠት በማሰብ ለእርቅ ስል ከሌሎች የፓርቲዉ መሪዎች ጋር ተስማማቼ ሰኔ 11 ቀን 1999 ዓ .ም በተጻፈው ሰነድ በሽማግሌዎች አማካኝነት ይቅርታ ጠይቄያለሁ። ይህ ብፈልግም ልለዉጠዉ የማልችለዉ ሐቅ ነዉ።»
ስትል በግለጽ ይቅርታ እንደጠየቀችና የተሰማማችበትን እንዳልካደች በገሃድ አሳዉቃለች። ወ /ት ብርቱካን «ይቅርታ ጠይቂያለሁ» ብላ በአደባባይ ጽፋ፣ አቶ መለስ ዜናዊ ግን «ይቅርታ አልጠየኩም» ብላለች ማለታቸዉ «እሳት አያቅጥለም» የሚል አይነት እራስን የሚያስገምት፣ የድርቅና አባባል ካልሆነ በቀር የአንድ አገር መሪ ነኝ እንዲሁም አህጉርን እወክላለሁ በማለት ከታላላቅ መሪዎች ጋር ፎቶግራፍ ከሚነሳ ግለሰብ የሚጠበቅ አይደለም።
ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳና ጓደኞቻቸዉ የይቅርታዉን ሰነድ ከመፈረማቸዉ በፊት በአገር ሽማግሌዎች በኩል የደረሰቻዉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልእክት «ይህ ሰነድ ከተፈረመ የሥራ አስፈጻሚ ሥልጣኔን ተጠቅሜ ክሱ እንዲቋረጥ አደርጋለሁ» የሚል ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ቃላቸዉን አላከበሩም። የፍርድ ሂደቱ እንዲቀጥል ተደርጎ በእሥረኞች ላይ የእድሜ ልክ እሥራት ሊበየንባቸዉ ችሏል።
ታዲያ ቃል የጣሰዉና ስምምነቱ ያላከበረዉ ማን ነዉ ? ቃል የተገባዉን የጣሰችዉ፣ ስምምነቷን ያላከበረችዉ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ሳትሆን አቶ መለስ ዜናዊ እራሳችዉ አይደሉምን ?
ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ፣ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ያላደረገችዉን አደረገች ብለዉ መክሰስ ሳያንሳቸዉ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ «ፈረንጆች ወይም ደጋፊዎቼ ያስፈቱኛል» ብላ እንደተታለለችም ይናገራሉ።
ከሶስት አመታት በፊት ቃሊቲ እሥር ቤት የነበረች ጊዜ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ለቀድሞ የአሜሪካ ቻርጅ ዳፌር ቪኪ ሃደልሰን የጻፉችዉን አቶ መለስ ዜናዊ ቢያነቡ ኖሮ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ በፈረንጆች ላይ ምንም አይነት እምነት እንደሌላትና በነርሱ ላይ የማትደገፍ መሆኗን ባወቁ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስተሩ በተሳሳተ መንገድ እንዳሉትም፣ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅስ ወደ ቃሊቲ እሥር ቤት ስትገባ ደጋፊዎቼ ያስፈቱኛል በሚል ተስፋም አልነበረም። ወደ ቃሊቲ የገባችዉ እዉነትን ዉሸት ፣ ዉሸትን እዉነት በማለት፣ ክብሯንና ነጻነቷን አሳልፋ ከመስጠት፣ መሞትን ስለመረጠች ነዉ። ይህ ባይሆን ኖሮ ለስድስት ወራት የአቶ መለስ ዜናዊ መንግስት በነፍሰ ገዳዮች ላይ እንኳን ባልታየ ሁኔታ ለስድስት ወራት በጨለማ ቤት ዉስጥ እንድትቀመጥና የስነ ልቦና ቶርቸር ሰለባ እንድትሆን ባደረገ ጊዜና የአገር ሽምግሌዎች በቃሊቲ ሲጎበኟት « ከእሥር ቤት ልዉጣ እንጂ መንግስት የሚጠይቀኝ ሁሉ አደርጋለሁ» ብላ ለፍቃዳቸዉና ለሽፍጣቸዉ ተንበርክካ፣ እራሷንና ሕሊናዋን ሽጣ ከቃሊቲ እሥር ቤት በወጣች ነበር።
በዚህ በጋዜጣዊ መግለጫ አቶ መለስ ዜናዊ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእሥር ቤት እንደማትወጣም በይፋ ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት በዋናነት የተቃዋሚዉን እንቅስቃሴ ተስፋ ለማስቆረጥ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አንድ የረሱት ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር እንደማናችንም ስጋ ለባሽ እንደሆኑና የርሳቸዉ ቃል የእግዚአብሄር ቃል እንዳልሆነ ነዉ። ወሳኙ እርሳችዉ ሳይሆኑ ወሳኙ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም በሰማይ የሚኖረዉ ታላቁ እግዚአብሄር ነዉ።
በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአደባባይ የሚሰጧቸዉ ከእዉነት የራቁ አሳዛኝ መግለጫዎች እራሳቸዉንና ድርጅታቸዉ ከማስገመትና አገርን ከመጉዳት ዉጭ የሚያመጣዉ ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለ ተረድተዉ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ እንዲፈቱ እንጠይቃለን። ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳን በማሰር የሚገኝ አንዳች የፖለቲካ ጥቅም ሊኖር አይችለም። ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳን በማሰር ይህ መንግስት ጊዚያዊ ጥቅም ያገኘና ሥልጣኑን ለማራዘም የቻለ ሊመስለዉ ይችላል። ነገር ግን አንዷን ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳን በማሰሩ በአሥር ሚሊይኖች የሚቆጠሩ ብርቱካን ሚደቅሳዎችን ነዉ የወለደዉ። ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ በእሥር ቤት በቁየች ቁጥር የፖለቲካዉ ቀዉስ የበለጠ ከመካረሩም ባሻገር ለሰላምና ለብሄራዊ እርቅ አመቺ ሁኔታ እንዳይፈጠር ያደርጋል።
ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ወንጀለኛ አይደለችም። ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሕሊና እሥረኛ ናት። ወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከዉርደት ክብርን፣ ከባርነት ነጻነትን፣ ከዉሸት እዉነትን፣ ከጥላቻ ፍቅርን፣ ከአስመሳይነት ሐቀኝነት የመረጠችና ሌሎች ኢትዮጵያዉያንን አሳልፋ ከመስጠት ይልቅ እራሷን ለሕዝብ ጥቅም አሳልፋ የሰጠች ዳግማዊት ጣይቱ ብጡል ታላቅ የኢትዮጵያ ልጅ ናት።
በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የምንኖር ኢትዮጵያዊያን ሁሉ፣ ዘር ጎሳ ኃይማኖት ጾታ እድሜ የፖለቲካ አስተሳሰብ የትምህርት ደረጃ ሳይከፋፍለን ለዜጎች መብት፣ ለወ /ት ብርቱካን ሚደቅሳና ሌሎች የሕሊና እሥረኞች መፈታትና ለአንዲት ኢትዮጵያ አንድነትና ደህንነት በጋራ እንድንቆም ጥሪ እናቀርባለን።
“ብርቱካንና ሁሉም የህሊና እስረኞች ይፈቱ” ግብረሀይል |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ተድላ ሀይሉ

Joined: 17 Mar 2006 Posts: 1716
|
Posted: Thu Dec 24, 2009 11:19 pm Post subject: |
|
|
---
Last edited by ተድላ ሀይሉ on Thu Dec 24, 2009 11:34 pm; edited 1 time in total |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ተድላ ሀይሉ

Joined: 17 Mar 2006 Posts: 1716
|
Posted: Thu Dec 24, 2009 11:25 pm Post subject: |
|
|
ብርቄነህ :-
"ግመል ሰርቆ አጎንብሶ ::" አሉ :: የአንተ ነገር እንደዚያ ነው :: ስለ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሣ የግፍ እሥር በእውነት ከልብህ የተቆረቆርክ መስሎኝ ነበር :: ለካ የአንተ የተሸፈነ ዓላማ ሌላ ኖርዋል
ለማንኛውም ብርቱካንን ለማስፈታት ደፈ ቀና በማለት ላይ ያሉት ጓዶቿ በሣህሌ (ስዬ ) አንጃ ተባባሪ ክሥ ምክንያት ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 15 ቀን 2002 ዓ .ም . በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በእሥር ላይ ናቸው :: በዚህ አጋጣሚ አንተ እና አንተን መሠል የሣር ውስጥ እባቦች እንኳን ደስ ያላችሁ
ተድላ
ምንጭ :- ብርቱ ቃሌ :: የመርህ ይከበር 5 አባላት በቦሌ ክ /ከተማ ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
| Code: | የመርህ ይከበር 5 አባላት በቦሌ ክ /ከተማ ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ያለው ህገ ወጡ የሥራ አስፈፃሚ ቡድን ለቦሌ ክፍለ ከተማ ገርጂ ፖሊስ ጣቢያ 13 የመርህ ይከበር አባላትን መክሰሱን መዘገባችን ይታወቀል፡፡
በዚሁ መሰረት ፖሊስ በአቶ ንጉሴ ነውጤ (የአንድነት ህግና ሥነ -ሥርዓት ጉዳይ ሀላፊ ) አማካኝነት መጥሪያ የላከ ሲሆን በዚሁ መሰረት መጥሪያው የደረሳቸው አምስት አባላት ናቸው፡፡
1. አቶ የሺዋስ አሰፋ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባልና የወጣቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ )
2. አቶ ወሮታው ዋሴ (በአንድነት የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ሰብሳቢ )
3. ወ /ት ሃና ዋለልኝ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል )
4. አቶ አለባቸው አያሌው (በአንድነት የደቡብ ቀጠና አስተባባሪ )
5. አቶ ፋኑኤል ደጌ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል )
አምስቱ አባላት በደረሳቸው መጥሪያ መሰረት ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2002 ዓ .ም ጠዋት 3፡ 00 ሰዓት ላይ ፖሊስ ጣቢያ የደረሱ ሲሆን ሆኖም ግን ፖሊስ ይህ ዜና እስከተሰራበት ከቀኑ 9፡ 10 ድረስ አለመልቀቁን ለማወቅ ተችሏል፡፡ |
|
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
የዋርካው ሚሊሻ

Joined: 25 Nov 2009 Posts: 6
|
Posted: Fri Dec 25, 2009 4:42 pm Post subject: |
|
|
| ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው: | ብርቄነህ :-
"ግመል ሰርቆ አጎንብሶ ::" አሉ :: የአንተ ነገር እንደዚያ ነው :: ስለ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሣ የግፍ እሥር በእውነት ከልብህ የተቆረቆርክ መስሎኝ ነበር :: ለካ የአንተ የተሸፈነ ዓላማ ሌላ ኖርዋል
ለማንኛውም ብርቱካንን ለማስፈታት ደፈ ቀና በማለት ላይ ያሉት ጓዶቿ በሣህሌ (ስዬ ) አንጃ ተባባሪ ክሥ ምክንያት ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 15 ቀን 2002 ዓ .ም . በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በእሥር ላይ ናቸው :: በዚህ አጋጣሚ አንተ እና አንተን መሠል የሣር ውስጥ እባቦች እንኳን ደስ ያላችሁ  |
ተድላ ትንሽ ቢዘገይም አሁን መንቃትህ ጠቃሚ ነው :: ምስጋናዬ ይድረስህ መልካም የፈረንጆች አዲስ አመት ይሁንልህ !!!!! |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
ብርቄነህ

Joined: 22 Jan 2009 Posts: 306
|
Posted: Mon Dec 28, 2009 7:12 pm Post subject: |
|
|
| ተድላ ሀይሉ እንደጻፈ(ች)ው: | ብርቄነህ :-
"ግመል ሰርቆ አጎንብሶ ::" አሉ :: የአንተ ነገር እንደዚያ ነው :: ስለ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሣ የግፍ እሥር በእውነት ከልብህ የተቆረቆርክ መስሎኝ ነበር :: ለካ የአንተ የተሸፈነ ዓላማ ሌላ ኖርዋል
ለማንኛውም ብርቱካንን ለማስፈታት ደፈ ቀና በማለት ላይ ያሉት ጓዶቿ በሣህሌ (ስዬ ) አንጃ ተባባሪ ክሥ ምክንያት ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 15 ቀን 2002 ዓ .ም . በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በእሥር ላይ ናቸው :: በዚህ አጋጣሚ አንተ እና አንተን መሠል የሣር ውስጥ እባቦች እንኳን ደስ ያላችሁ
ተድላ
ምንጭ :- ብርቱ ቃሌ :: የመርህ ይከበር 5 አባላት በቦሌ ክ /ከተማ ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
| Code: | የመርህ ይከበር 5 አባላት በቦሌ ክ /ከተማ ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ያለው ህገ ወጡ የሥራ አስፈፃሚ ቡድን ለቦሌ ክፍለ ከተማ ገርጂ ፖሊስ ጣቢያ 13 የመርህ ይከበር አባላትን መክሰሱን መዘገባችን ይታወቀል፡፡
በዚሁ መሰረት ፖሊስ በአቶ ንጉሴ ነውጤ (የአንድነት ህግና ሥነ -ሥርዓት ጉዳይ ሀላፊ ) አማካኝነት መጥሪያ የላከ ሲሆን በዚሁ መሰረት መጥሪያው የደረሳቸው አምስት አባላት ናቸው፡፡
1. አቶ የሺዋስ አሰፋ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባልና የወጣቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ )
2. አቶ ወሮታው ዋሴ (በአንድነት የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ሰብሳቢ )
3. ወ /ት ሃና ዋለልኝ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል )
4. አቶ አለባቸው አያሌው (በአንድነት የደቡብ ቀጠና አስተባባሪ )
5. አቶ ፋኑኤል ደጌ (በአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል )
አምስቱ አባላት በደረሳቸው መጥሪያ መሰረት ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2002 ዓ .ም ጠዋት 3፡ 00 ሰዓት ላይ ፖሊስ ጣቢያ የደረሱ ሲሆን ሆኖም ግን ፖሊስ ይህ ዜና እስከተሰራበት ከቀኑ 9፡ 10 ድረስ አለመልቀቁን ለማወቅ ተችሏል፡፡ |
|
| Quote: | ብርቄነህ :-
"ግመል ሰርቆ አጎንብሶ ::" አሉ :: የአንተ ነገር እንደዚያ ነው :: ስለ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሣ የግፍ እሥር በእውነት ከልብህ የተቆረቆርክ መስሎኝ ነበር :: ለካ የአንተ የተሸፈነ ዓላማ ሌላ ኖርዋል |
የሚያደርጉትን ባለማወቅም ሆነ እያወቁ በጥቅም በመገዛት ወያኔን ከሚያገልግሉት ውስጥ ግምባር ቀደሙ ሰው መሆንህን ስላወኩኝ ካሁን በኍላ መልስ ልሰጥህ አልሞክርም :: የሚገባህ መስሎኝ ከዚህ በፊት ነግሬህ ነበር :: አንተ ስዬ ምናምን እያልክ የወያኔን ተልዕኮ ተወጣ :: እኔ ግን ብርቱካን እንድትፈታ መጮሄን እቀጥልበታለሁ :: |
|
|
|
This message expresses the views and opinions of the author and not necessarily
those of CyberEthiopia, its staff or its affiliates. If you think this message
is inappropriate or violates our rules and regulations , please notify the Administrators by clicking on the report button below.
|
| Back to top |
|
|
|
|
 |
|